44
|ገጽ 1 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005 FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ 3 ቀን 2005 የረቡዕ እትም ቅፅ 18 ቁጥር 15/ 1317| አዲስ አበባ ኢትዮጵያ | ጳጉሜን 6 ቀን 1987 ተመሠረተ |ዋጋ ብር 7.00 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ወደ ገጽ 11 ዞሯል ሟች ቤተልሔም ሰለሞን አማራጭ ሐሳብና አማራጭ ጥንካሬ ያለው ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ይፈለጋል! የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ ነገ ከአምባሳደሮች ጋር ይተዋወቃሉ በዮሐንስ አንበርብር በርካቶች ያልተጠበቀ ያሉትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሹመት ያገኙት የቀድሞው የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም፣ በአዲስ አበባ ከሚገኙ የውጭ አገር ዲፕሎማቶች ጋር በነገው ዕለት በይፋ ይተዋወቃሉ:: ዶክተር ቴድሮስ ከ1998 ዓ.ም. ጀምሮ በጤና ጥበቃ ሚኒስትርነት ሲያገለግሉ መቆየታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አቅራቢነት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል:: የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሕልፈት ተከትሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ኃይለ ማርያም በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሲሾሙ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሥልጣናቸው ክፍት ሆኖ ለወራት መቆየቱ ይታወሳል:: ይሁን እንጂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታነት ሲሠሩ የነበሩት አምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ በተጠባባቂነት እንዲሠሩ በመደረጉ፣ እንዲሁም በውጭ ዲፕሎማሲ መስክ ለረጅም ዓመታት ባከበቱት ልምድ የተነሳ የሚኒስትርነቱን ሥልጣን እሳቸው ይወስዱታል ገቢዎች ባለሥልጣን ከ30 ሺሕ የካሽ ሬጂስተር መሣሪያዎች መረጃ እያገኘ አይደለም በዮሐንስ አንበርብር የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በሕግ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ግብር ከፋዮች የሽያጭ መመዝገቢያ መሣርያ በመጠቀም ሽያጫቸውን በቀጥታና ግብይቱ በተፈጸመበት ወቅት መረጃ የሚያቀብል ሥርዓትን ዘርግቶ፣ በዚህም መሠረት ከ60 ሺሕ በላይ መሣርያዎች ጥቅም ላይ ቢውሉም፣ 30 ሺሕ የሚሆኑት በቴሌ የኔትወርክ ችግር ምክንያት በአሁኑ ወቅት ለባለሥልጣኑ መረጃ እያቀረቡ አይደለም:: በዚህ ችግር ምክንያት ግብር ከፋዮች የተጠራቀመ ሽያጫቸውን በወረቀት በማተም ለባለሥልጣኑ የማቅረብ ተጨማሪ ሥራ ውስጥ በመግባታቸው፣ የባለሥልጣኑ ሠራተኞችም በወረቀት ሥራ ብዛት ተጠምደዋል:: የባለሥልጣኑ የሩብ ዓመት የሥራ ክንውን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በእሳቸው የቀድሞ ሥልጣን ላይ ከተሰየሙት ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ጋር በሟቹ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ 20ኛ ዓመት በዓለ ሲመት ላይ ፎቶ ሪፖርተር/ፋይል በታምሩ ጽጌ የመጀመርያ ልጇን በቀዶ ሕክምና ከተገላገለች በኋላ ደም ፈሷት ሕይወቷ ያለፈው የ27 ዓመት ወጣት የቀብር ሥርዓቷ ባለፈው ቅዳሜ፣ እሑድና ከትናንት በስቲያ ሰኞ የመፈጸሙ ጉዳይ እያነጋገረ ነው:: ሟች ቤተልሔም ሰለሞን ልጅ ወልዳ ለመሳም ዘጠኝ ወራትን ስትጠብቅና የእርግዝናዋንም ሁኔታ ስትከታተል ቆይታ የመውለጃዋ ዕለት በመድረሱ፣ ጎፋ ማዞሪያ ወደሚገኘው ሮያል የጽንስና የማኅፀን ሕክምና ከፍተኛ ክሊኒክ የሄደችው ኅዳር 27 ቀን 2005 ዓ.ም. ነበር:: ክትትል ስታደርግበት የነበረው ክሊኒክ ተቀብሎአት ወደ ማዋለጃ ክፍል ካስገባት በኋላ የምጥ መርፌ ቢወጋትም፣ በዕለቱ ልትወልድ አለመቻሏንና ወደ ቤቷ መመለሷን ወላጅ እናቷ ወይዘሮ በለጡ አበበና ባለቤቷ አቶ ፍስሐ እሸቴ ገልጸዋል:: ቤተሰቦቿ እንደሚሉት፣ ቤተልሔም ምጧ እየተፋፋመ በመምጣቱ ኅዳር 28 ቀን 2005 ዓ.ም. ተመልሳ ወደ ክሊኒኩ ትሄዳለች:: የክሊኒኩ ሐኪሞች ተቀብለዋት ወደ ማዋለጃ ክፍል ካስገቧት ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ፣ ቤተሰቦቿ ተጠርተው “እንኳን ደስ ያላችሁ፤ በሰላም ተገላግላለችና የሕፃኗን ማቀፊያ አምጡ፤” ይባላሉ:: በክሊኒኩ የተገኙት እናቷና ባለቤቷ ደስታቸውን በእልልታና እርስ በርስ በመሳሳም ገልጸው ለጥቂት ደቂቃዎች እንደቆዩ፣ ቤተልሔም “እናቴን፣ ባለቤቴንና ልጄን አሳዩኝ፤” ብላለች ተባሉና ሁሉም ገቡ:: ቤተልሔም ከማደንዘዣ ነቅታ በደንብ እንዳነጋገረቻቸው ተናግረው፣ “ጠብቁ አሁን ትወጣለች” በመባላቸው ሕፃኗን ይዘው ከነበረችበት ክፍል ወጥተው መጠባበቅ መጀመራቸውን አስረድተዋል:: ሐኪሞቹ “ትንሽ ቆዩና ባለቤቷን ጠሩት” የሚሉት የቤተልሔም እናት፣ እሳቸው ግራ ገብቷቸው በመጠባበቅ ላይ እያሉ፣ ባለቤቷ መኪናቸውን ይዘው ሲወጡ መመልከታቸውንና በዚያው መቅረታቸውን ተናግረዋል:: ልጃቸው ምን እንደሆነች ያላወቁትና ግራ ተጋብተው ሲንቆራጠጡ ለነበሩት የቤተልሔም እናት፣ አንዲት ነርስና በሁለት ቀናት ልዩነት ሦስት ጊዜ ቀብሯ የተፈጸመው ወላድ ጉዳይ እያነጋገረ ነው አስከሬኗ ከመቃብር ወጥቶ ተገኝቷል

reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

Embed Size (px)

DESCRIPTION

3 ቀን 2005 |ገጽ 1ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ www.ethiopianreporter.com FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRITበውስጥ ገጽ2ወደ ገጽ 11 ዞሯልታህሳስ 3 ቀን 2005

Citation preview

Page 1: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 1 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRITነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ

በውስጥ

ገጽ 2

ወደ ገጽ 11 ዞሯል

ታህሳስ 3 ቀን 2005

የረቡዕ እትም

ቅፅ 18 ቁጥር 15/ 1317| አዲስ አበባ ኢትዮጵያ | ጳጉሜን 6 ቀን 1987 ተመሠረተ |ዋጋ ብር 7.00

ወደ ገጽ 11 ዞሯል

ወደ ገጽ 11 ዞሯል ሟች ቤተልሔም ሰለሞን

አማራጭ ሐሳብና አማራጭ ጥንካሬ ያለው ተቃዋሚ

የፖለቲካ ፓርቲ ይፈለጋል!

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ ነገ ከአምባሳደሮች ጋር ይተዋወቃሉበዮሐንስ አንበርብር

በርካቶች ያልተጠበቀ ያሉትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሹመት ያገኙት የቀድሞው የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም፣ በአዲስ አበባ ከሚገኙ የውጭ አገር ዲፕሎማቶች ጋር በነገው ዕለት በይፋ ይተዋወቃሉ::

ዶክተር ቴድሮስ ከ1998 ዓ.ም. ጀምሮ በጤና ጥበቃ ሚኒስትርነት ሲያገለግሉ መቆየታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አቅራቢነት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል::

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሕልፈት ተከትሎ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ኃይለ ማርያም በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሲሾሙ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሥልጣናቸው ክፍት ሆኖ ለወራት መቆየቱ ይታወሳል::

ይሁን እንጂ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታነት ሲሠሩ የነበሩት አምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ በተጠባባቂነት እንዲሠሩ በመደረጉ፣ እንዲሁም በውጭ ዲፕሎማሲ መስክ ለረጅም ዓመታት ባከበቱት ልምድ የተነሳ የሚኒስትርነቱን ሥልጣን እሳቸው ይወስዱታል

ገቢዎች ባለሥልጣን ከ30 ሺሕ የካሽ ሬጂስተር መሣሪያዎች መረጃ እያገኘ አይደለምበዮሐንስ አንበርብር

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በሕግ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ግብር ከፋዮች የሽያጭ መመዝገቢያ መሣርያ በመጠቀም ሽያጫቸውን በቀጥታና ግብይቱ በተፈጸመበት ወቅት መረጃ የሚያቀብል ሥርዓትን ዘርግቶ፣ በዚህም መሠረት ከ60 ሺሕ በላይ መሣርያዎች ጥቅም ላይ ቢውሉም፣ 30 ሺሕ የሚሆኑት በቴሌ የኔትወርክ ችግር ምክንያት በአሁኑ ወቅት ለባለሥልጣኑ መረጃ እያቀረቡ አይደለም::

በዚህ ችግር ምክንያት ግብር ከፋዮች የተጠራቀመ ሽያጫቸውን በወረቀት በማተም ለባለሥልጣኑ የማቅረብ ተጨማሪ ሥራ ውስጥ በመግባታቸው፣ የባለሥልጣኑ ሠራተኞችም በወረቀት ሥራ ብዛት ተጠምደዋል::

የባለሥልጣኑ የሩብ ዓመት የሥራ ክንውን

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በእሳቸው የቀድሞ ሥልጣን ላይ ከተሰየሙት ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ጋር በሟቹ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ 20ኛ ዓመት በዓለ ሲመት ላይ ፎቶ ሪፖርተር/ፋይል

በታምሩ ጽጌ

የመጀመርያ ልጇን በቀዶ ሕክምና ከተገላገለች በኋላ ደም ፈሷት ሕይወቷ ያለፈው የ27 ዓመት ወጣት የቀብር ሥርዓቷ ባለፈው ቅዳሜ፣ እሑድና ከትናንት በስቲያ ሰኞ የመፈጸሙ ጉዳይ እያነጋገረ ነው::

ሟች ቤተልሔም ሰለሞን ልጅ ወልዳ ለመሳም ዘጠኝ ወራትን ስትጠብቅና የእርግዝናዋንም ሁኔታ ስትከታተል ቆይታ የመውለጃዋ ዕለት በመድረሱ፣ ጎፋ ማዞሪያ ወደሚገኘው ሮያል የጽንስና የማኅፀን ሕክምና ከፍተኛ ክሊኒክ የሄደችው ኅዳር 27 ቀን 2005 ዓ.ም. ነበር::

ክትትል ስታደርግበት የነበረው ክሊኒክ ተቀብሎአት

ወደ ማዋለጃ ክፍል ካስገባት በኋላ የምጥ መርፌ ቢወጋትም፣ በዕለቱ ልትወልድ አለመቻሏንና ወደ ቤቷ መመለሷን ወላጅ እናቷ ወይዘሮ በለጡ አበበና ባለቤቷ አቶ ፍስሐ እሸቴ ገልጸዋል::

ቤተሰቦቿ እንደሚሉት፣ ቤተልሔም ምጧ እየተፋፋመ በመምጣቱ ኅዳር 28 ቀን 2005 ዓ.ም. ተመልሳ ወደ ክሊኒኩ ትሄዳለች:: የክሊኒኩ ሐኪሞች ተቀብለዋት ወደ ማዋለጃ ክፍል ካስገቧት ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ፣ ቤተሰቦቿ ተጠርተው “እንኳን ደስ ያላችሁ፤ በሰላም ተገላግላለችና የሕፃኗን ማቀፊያ አምጡ፤” ይባላሉ:: በክሊኒኩ የተገኙት እናቷና ባለቤቷ ደስታቸውን በእልልታና እርስ በርስ በመሳሳም ገልጸው ለጥቂት ደቂቃዎች እንደቆዩ፣ ቤተልሔም “እናቴን፣

ባለቤቴንና ልጄን አሳዩኝ፤” ብላለች ተባሉና ሁሉም ገቡ:: ቤተልሔም ከማደንዘዣ ነቅታ በደንብ እንዳነጋገረቻቸው ተናግረው፣ “ጠብቁ አሁን ትወጣለች” በመባላቸው ሕፃኗን ይዘው ከነበረችበት ክፍል ወጥተው መጠባበቅ መጀመራቸውን አስረድተዋል:: ሐኪሞቹ “ትንሽ ቆዩና ባለቤቷን ጠሩት” የሚሉት የቤተልሔም እናት፣ እሳቸው ግራ ገብቷቸው በመጠባበቅ ላይ እያሉ፣ ባለቤቷ መኪናቸውን ይዘው ሲወጡ መመልከታቸውንና በዚያው መቅረታቸውን ተናግረዋል::

ልጃቸው ምን እንደሆነች ያላወቁትና ግራ ተጋብተው ሲንቆራጠጡ ለነበሩት የቤተልሔም እናት፣ አንዲት ነርስና

በሁለት ቀናት ልዩነት ሦስት ጊዜ ቀብሯ የተፈጸመው ወላድ ጉዳይ እያነጋገረ ነው

አስከሬኗ ከመቃብር ወጥቶ ተገኝቷል

Page 2: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

በጳጉሜን 6 1987 ተጀመረ በሳምንት ሁለት ጊዜ የሚታተም አድራሻ፡- ከቦሌ መድኃኒዓለም ወደ ብራስ ሆስፒታል በሚወስደው መንገድ ከቦሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል አጠገብ ስልክ 0910-885206/ 011-661 61 79/85/87/011-8614339 ፋክስ: 011-661 61 89

አድራሻ፡- ቦሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 03 የቤት ቁጥር 2347 ፖስታ 7023 አ.አ ኢትዮጵያ

ማስታወቂያ ሽያጭና ስርጭት 0910 885206/ 011 6 61 61 79/ 85

[email protected] E-mail: [email protected]

Website: www.ethiopianreporter.com

ዋና ሥራ አስኪያጅ፡ አማረ አረጋዊዋና አዘጋጅ፡ መላኩ ደምሴአራዳ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 13/14 የቤት ቁ. 481ምክትል ዋና አዘጋጅ፡ ዘካሪያስ ስንታየሁከፍተኛ አዘጋጅ፡ ዳዊት ታዬ አዘጋጆች፡ ሔኖክ ያሬድ ጌታቸው ንጋቱ

ምሕረት ሞገስ ኃይሌ ሙሉ

ረዳት አዘጋጆች፡ ታደሰ ገ/ማርያም ምሕረት አስቻለው ታምሩ ጽጌ የማነ ናግሽ

ዋና ግራፊክ ዲዛይነር፡ ይበቃል ጌታሁንከፍተኛ ግራፊክ ዲዛይነር፡ ቴዎድሮስ ክብካብግራፊክ ዲዛይነሮች፡ ፀሐይ ታደሰ ፋሲካ ባልቻ እንዳለ ሰሎሞን ስሜነህ ሲሳይ ቢኒያም ግርማ ነፃነት ያዕቆብ ቤዛዬ ቴዎድሮስ

ዋና ፎቶ ግራፈር ናሆም ተሰፋዬፎቶ ግራፈሮች፡ ታምራት ጌታቸው መስፍን ሰሎሞን

ካርቱኒስት፡ ኤልያስ አረዳ

በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር (ኤም.ሲ.ሲ) ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር

እየታተመ የሚወጣ ጋዜጣ

ረቡዕ ታህሳስ 3 ቀን 2005

ርእሰ አንቀጽ

ከፍተኛ ሪፖርተሮች፡ ደረጀ ጠገናው ብርሃኑ ፈቃደ ውድነህ ዘነበ፣ ሰሎሞን ጎሹሪፖርተር፡ ምዕራፍ ብርሃኔማርኬቲንግ ማናጀር፡ እንዳልካቸው ይማምሴልስ፡ ቤዛዊት ፀጋዬ' Hና Ó`T' w\¡ S<K<Ñ@�' IK=ና ከuደ፣ ብሩክ ቸርነትማስታወቂያ ፕሩፍሪደር፡መሳይ ሰይፉ፤ ኤፍሬም ገ/መስቀል፤ ዳዊት ወርቁኮምፒውተር ጽሑፍ፡ ብርቱካን አባተ፣ ሄለን ይታየው፣ ፣ ፍሬሕይወት ተሰማ፣ ማስታወቂያ ፅሁፍ እስከዳር ደጀኔ፣ መሠረት ወንድሙ፣ ራሔል ሻወልሕትመት ክትትል፡ ተስፋዬ መንገሻ፣ የየሱስወርቅ ማሞ፣ ገዛኸኝ ማንደፍሮዌብ ሳይት፡ ቤዛዊት ተስፋዬ፣ ቢኒያም ሐይሉ

ማስታ

ወቂያ

አገራችን ኢትዮጵያ ምን እንድትሆን ትፈልጋላችሁ ብንባል ቀጥተኛውና ቀልጣፋው መልሳችን የበለፀገችና ዲሞክራሲያዊት አገር እንድትሆን እንፈልጋለን ነው:: ልማትና ዲሞክራሲ ጐን ለጐን ተያይዘውና ተሳስረው የሚታዩባት አገር እንድትሆን እንፈልጋለን::

ልማት እንጂ ዲሞክራሲ አንፈልግም የሚለውን አንቀበልም:: ዲሞክራሲ እንጂ ልማት አንፈልግም የሚለውንም አንቀበልም:: ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት፣ መንግሥትና ፖለቲካ እንፈልጋለን::

ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንፈልጋለን ስንል አንዱ መገለጫው የተለያዩ ሐሳቦች የሚንሸራሸሩበት ሥርዓት እውን ማድረግ ነው:: ለአገር የሚጠቅም የተሻለ ሐሳብ አለን የሚሉ ኃይሎች የሚሰባሰቡበትና የሚደራጁበት የፖለቲካ ፓርቲ መፍጠርና ሥልጣን ለመያዝ መወዳደር መብት መሆኑን የሚያረጋግጥ ሥርዓት እውን ማድረግ ማለት ነው::

ስለሆነም የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖር ለአንድ አገር ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን መሆን ወሳኝ ነው:: ሐሳቦች እርስ በርስ ይወዳደራሉ፤ ይታገላሉ:: ሕዝቡም የተሻለውን ሐሳብ ይመርጣል:: በሕዝብ ድምፅ የተመረጠውም አገሪቱን እንዲመራ ኃላፊነት ይሰጠዋል ማለት ነው::

በዚህ ዙሪያ ሕዝብም፣ መንግሥትም፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በሥነ ሐሳብ ደረጃ ልዩነት የላቸውም:: ሕዝብ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ኖረው ይወዳደሩ ብሎ ያምናል:: በሕገ መንግሥቱም ሰፍሯል::

በተግባር ግን የጠንካራ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ትግል፣ ፉክክርና ውድድር ማየት አልቻልንም:: ጠንካራ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ እውን ማድረግ አልተቻለም:: ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስፈላጊ የሆነው ጠንካራ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ በተግባር በኢትዮጵያ እውን መሆን አልቻለም::

ለምን?

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጠንካራ መሆን ያልቻልነው ገዥው ፓርቲ እንዳንጠናከር ስላደረገን ነው የሚል መከራከሪያ ሊያቀርቡ ይችላሉ:: ገዥው ፓርቲ ይህንን በተመለከተ ንፁህ ነው ብለን አንከራከርም:: የፈጠረው ችግርና ጫና የለምም አንልም:: ነገር ግን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያልተጠናከሩበት ዋነኛው ምክንያት በራሳቸው ድክመት፣ ጉድለትና የብቃት ማነስ ነው እንላለን:: ከማንም በፊት ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ ላለመኖሩ ተጠያቂ የምናደርገው ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ራሳቸውን ነው::

ለምን?

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጠንካራ፣ ግልጽና፣ ይፋ የሆነ አማራጭ ሐሳብ ለሕዝብ አላቀረቡም::

ጠንካራ ሐሳብ አለመኖር ብቻ ሳይሆን ጠንካራ አደረጃጀትና ጠንካራ እንቅስቀሴም አያሳዩም::

ተቃዋሚ ፓርቲዎች በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኙና እንዲከበሩ አማራጭ ሐሳብ ማቅረብ አለባቸው::

ገዥው ፓርቲ ትክክልም ይሁን ስህተት ለእያንዳንዱ ጉዳይ በፖለቲካ መስመር፣ በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ዘርፎች ዕቅዶች አሉት:: ግብርናን፣ ኢንዱስትሪን፣ ትራስፖርትን፣ ዲፕሎማሲን፣ መገናኛ ብዙኅንን፣ ምርጫን፣ ዲሞክራሲን፣ ልማትን፣ ወዘተ እንዲህ አደርጋለሁ፤ ዕቅዴን እንዲህ እፈጽመዋለሁ፤ በዚህ ዓመት ይህ ይከናወናል ብሎ በግልጽ አቅርቧል::

የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች የለም እኛ ሥልጣን ብንይዝ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በፕሬስ፣ በዲሞክራሲ፣ በዲፕሎማሲ፣ ወዘተ እንዲህ እናደርጋለን፤ ይህንን ፖሊሲ እንከተላለን፤ አፈጻጸሙም እንዲህ ይሆናል፤ ውጤቱም እንዲህ እንዲሆን እንታገላለን ማለት ነበረባቸው::

ስለዚህ አንዱና ትልቁ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ድክመት አማራጭ ሐሳብ፣ አማራጭ ፕሮግራምና አማራጭ ስትራቴጂ በግልጽ ለሕዝቡ አለማቅረባቸው ነው::

ሁለተኛው ድክመታቸው አማራጭ አደረጃጀትና የእንቅስቃሴ ጥንካሬ አለማሳየታቸው ነው:: ለመሆኑ ተቃዋሚ ድርጅቶች አባሎቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ምን ያህል ይሆናሉ? ለመሆኑ ዓመታዊ ጉባዔ ያካሂዳሉ ወይ? ለመሆኑ በፓርቲያቸው ውስጥ ወቅቱን የጠበቀ ምርጫና ግምገማ ይካሄዳል ወይ? የውስጥ ኦዲት ይደረጋል ወይ? ግልጽነት አለ ወይ? ፓርቲውን ሁሌም የሚመራው አንድ ዓይነት ኃይል ነው? ወይስ መተካካት አለ? ወጣቶች በፓርቲው ውስጥ ምን ሚና አላቸው? ወዘተ የሚለው መታየት አለበት::

ሌላው ትልቁ ድክመት ይህ ነው:: ተቃዋሚ ፓርቲዎች በውስጣቸው ጥንካሬ አይታይም:: ዲሞክራሲያዊ ሕይወት አይንፀባረቅም:: መተካካት የሚባለው ፈጽሞ አይታወቅም::

ይህ የሚያሳየን አማራጭ ሐሳብ መኖሩ ብቻ ሳይሆን፣ አማራጭ ሐሳብ ተይዞም ወደ ድርጅታዊ እንቅስቃሴና ጥንካሬ ካልተቀየረ በሲዲና በወረቀት ብቻ ማሳየት አቅም አለመኖሩን ማሳያ ነው::

በአጠቃላይ ሲታይ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን መሆንና ጥንካሬ ሲባል ተቃዋሚ ፓርቲዎች እንዲጠናከሩ ያስፈልጋል:: በኢትዮጵያ ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ ባለመኖሩ ጉዳት እየደረሰ ነው:: በኢሕአዴግ ላይ ቅሬታ ያለው ወገን በግራም በቀኝም ሲያይ ጠንካራ ተቃዋሚ ስለማያገኝ፣ ኢሕአዴግን የሚተካ ኃይል ይኖራል ብሎ መተማመን አልቻለም:: ምን ተቃዋሚ አለና እያለ ተስፋ እየቆረጠ ነው::

በመሆኑም ተቃዋሚ ፓርቲዎች በሌላ ወገን ሳያሳብቡ መጀመሪያ ውስጣቸውን ይፈትሹ፤ ድክመታቸውን ይመኑ:: ብቁ ተቃዋሚ ለመሆን ይጣሩ:: ድክመታቸው ሲነገራቸው ለጥንካሬያቸው ስለሚበጅ በእጅጉ ያስቡበት:: የብቁ ተቃዋሚ የጥበብ መጀመሪያም አማራጭ ሐሳብና አማራጭ ጥንካሬ ለሕዝብ ማቅረብ ነው::

ይፈለጋል!

አማራጭ ሐሳብና አማራጭ ጥንካሬ ያለው ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ይፈለጋል!

Page 3: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 3 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ማስታ

ወቂያ

ወደ ገጽ 5 ዞሯልወደ ገጽ 5 ዞሯል

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የመድረክ አመራር በእስራት ተቀጡ ተቋርጦ የነበረው የፍትሕ ጋዜጣ

ዋና አዘጋጅ ክስ እንደገና ተጀመረበታምሩ ጽጌ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የውጭ ቋንቋ መምህርና የመድረክ ፓርቲ አመራር አቶ በቀለ ገርባና ሌሎች ስምንት ተከሳሾች፣ ከሦስት ዓመታት እስከ 13 ዓመታት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ትናንትና ተወሰነባቸው::

በሽብርተኝነት ወንጀል በፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የተመሠረተባቸውን ክስ ሲመረምር የሰነበተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ ወንጀል ችሎት ትናንትና በሰጠው የቅጣት ውሳኔ፣ አንደኛ ተከሳሽ የነበሩት አቶ በቀለ ገርባን በስምንት ዓመታት፣ የኦህኮ ፓርቲ አመራር የነበሩትን አቶ ኦልባና ሌሊሳን በ13 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ትዕዛዝ አስተላልፏል::

ሌሎቹ ተከሳሾች ማለትም ወልቤካ ለሜ፣ መሐመድ ቡሳ፣ ሐዋ ዋቆ፣ ደረጀ ከተማ፣ አዲሱ ሙከሪና ገልገሎ ቱፋ ከሦስት እስከ 12 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል:: አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ኦልባና ሌሊሳና አቶ ገልገሎ ቱፋ ለአራት ዓመታት ከማንኛውም ማኅበራዊ መብቶቻቸው ታግደዋል:: ሌሎቹም ለሁለት ዓመታት ታግደዋል::

አቶ በቀለ ገርባ በ2003 ዓ.ም. የተማሪዎች የመመረቂያ ጽሑፍ ሲመረምሩ በአጋጣሚ ያገኟቸውን ተማሪዎች፣ ‹‹ገዢውን መንግሥት መጣል አሁን ነው›› በማለትና በመመልመል ለኦነግ በመሥራትና ኦፌዴንን ከለላ በማድረግ የሽብር ተልዕኮ ሲፈጽሙ ነበር በማለት መከሰሳቸው ይታወሳል::

አቶ ኦልባናም በአምቦ ተማሪዎችን በመመልመልና ወደ ኦነግ እንዲገቡ በማደራጀት ፀረ ሽብር ተግባር ሲፈጽሙ እንደነበር፣ ሌሎቹም እስከ ኬንያ ድረስ በመሄድ ሥልጠና እንዲወስዱ በማድረግ፣ ከኦነግ ጋር በመሥራት የሽብር ተልዕኮ ሊፈጽሙ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ ማቅረቡ ይታወሳል:: ፍርድ ቤቱ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን መሠረት መከላከያ ቢያቀርቡም፣ የዓቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ሊያስተባብሉ አለመቻላቸውን በመግለጽ ጥፋተኛ ብሏቸዋል:: ዓቃቤ ሕግ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ያቀረበው የቅጣት ማክበጃ ቅጣቱ ከብዶ እንዲወሰን ነበር:: ተከሳሾቹ የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርቡ ሲጠየቁ አቶ በቀለ ጥፋተኛ አለመሆናቸውንና አድርገዋል በተባሉት ጉዳይ ላይ ምንም ነገር እንዳልፈጸሙ፣ ለኦሮሞ ሕዝብ ነፃነት ሲታገሉ ሕዝቡን በድለው ከሆነ ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ከመጠየቅና ባለቤታቸው በእሳቸው ምክንያት ከሥራ በመባረራቸው ልጆቻቸው ያለ ገቢ ከመኖራቸው በስተቀር፣ ምንም ያጠፉት ነገር እንደሌለ ገልጸዋል:: አቶ ኦልባናም ለምን እንደታሰሩ አለማወቃቸውን

ጋዜጠኛ ርዕዮተ ዓለሙ ለሰበር ያቀረበችው አቤቱታ ለውሳኔ ተቀጠረ

በታምሩ ጽጌ

ሦስት ክሶች ተመሥርተውበትና ዋስትና ተከልክሎ ለአራት ቀናት በማረሚያ ቤት ከቆየ በኋላ፣ ክሱ ተቋርጦ በነፃ የተሰናበተው የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ የተቋረጠው ክስ በድጋሚ ትናንትና ፍርድ ቤት ቀርቦበት በ50 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቀ::

ከነሐሴ 23 ቀን 2003 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት

በፍትሕ ጋዜጣ ላይ በራሱና በጽሑፍ አቅራቢዎች አምስት ጊዜያት ታትመው በወጡ መጣጥፎች ምክንያት ክስ ተመሥርቶበት፣ ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም. የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 16ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ዋስትና በመከልከሉ ማረሚያ ቤት እንዲቆይ መደረጉ ይታወሳል::

ክስ መሥርቶበት የነበረው የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ፣ ‹‹የማጣራው ምርመራ ስላለኝ እስከዚያው ድረስ ክሴን አቋርጫለሁ፤›› በማለት ነሐሴ 21 ቀን 2004 ዓ.ም. ለፍርድ ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ አማካይነት፣ ጋዜጠኛ ተመስገን ነሐሴ 22 ቀን 2004 ዓ.ም. ከእስር ተፈትቶ ነበር:: ዓቃቤ ሕግ ላለፉት ሦስት ወራት አቋርጦት በድጋሚ በተንቀሳቀሰው ክስ ውስጥ ጋዜጠኛ ተመስገን በተለያዩ ጊዜያት ዕትሞች ‹‹ሞት የማይፈሩ ወጣቶች፣ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን እስከ መጨፈር፣ የሁለተኛ ዜግነት ሕይወት እስከመቼና ሲኖዶስና መጅሊስ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ማጥመቂያ›› የሚሉ መጣጥፎች ማወጣቱ ተገልጿል::

በመሆኑም በወጡት መጣጥፎች ወጣቶችን ለአመፅ አነሳስቷል፣ ቀስቅሷል፣ ስም አጥፍቷል በሚል ነበር የመጀመሪያው ክስ የቀረበው:: አሁንም የቀረበው ክስ ይኼው ነው::

በትናንትናው ዕለት ዓቃቤ ሕግ ለምን ክሱን ማንቀሳቀስ እንደፈለገ እንዲያስረዳ ችሎቱ ጠይቆት፣ ፍትሕ ሚኒስቴር በአዋጅ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ክስን የማቋረጥና የመጀመር ሥልጣን እንዳልው ከመግለጽ ባለፈ በዝርዝር አላስረዳም:: ፍርድ ቤቱ በሁለተኛነት ክስ የተመሠረተበትና የፍትሕ አሳታሚ የሆነው ማስተዋል የሕትመትና የማስታወቂያ ድርጅትም እንዲቀርብ አዞ፣ ክሱ መቀጠል አለመቀጠሉን በሚመለከት ብይን ለመስጠት ለታህሳስ 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል::

ፍትሕ ጋዜጣ ሐምሌ 13 ቀን 2004 ዓ.ም. ለሕትመት ወደ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የገባ ቢሆንም፣ ‹‹ፍትሕ ሚኒስቴር እንዳታትም ብሎኛል›› በሚል ምክንያት ማተሚያ ቤቱ አላትምም ማለቱን መዘገባችን ይታወሳል:: ጋዜጣው በወቅቱ ለምን እንዳልታተመ እስካሁን በግልጽ የተገለጸ ነገር ባይኖርም፣ በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በነበሩት በአቶ መለስ ዜናዊ ሕመምና በአጠቃላይ በወቅቱ ስለነበሩበት ሁኔታዎች የሚያትት መጣጥፍ ይዞ ስለነበር፣ ሕዝብን

ዋስትና ተፈቅዶለት በ50 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቀ

በውድነህ ዘነበ

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በየጊዜው በሚካሄድ የአመራር ለውጥ መረጋጋት ለተሳነው አዳማ (ናዝሬት) ከተማ የተረጋጋ አስተዳደር እንዲኖረው የሚያስችል ዕቅድ መንደፉ ታወቀ::

በአዳማ ከተማ በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ አራት ከንቲባዎች ከሥልጣናቸው ተነስተዋል:: ከዚህ በተጨማሪም በአስተዳደሩ ሥር በሚገኙ መሥሪያ ቤቶች በተለያዩ እርከኖች ላይ የሚገኙ አመራሮችም ከቦታቸው ተነስተዋል::

ይህ ከፍተኛ ሹምሽር ከተማው የሚፈልገውን ዕድገትና ለውጥ ማምጣት እንዳያስችል አድርጓል በሚል፣ የክልሉ መንግሥት የከተማው አስተዳደር የተረጋጋና ብቃት ያላቸው አመራሮች እንዲመድቡ ከተማው ከክልሉ መንግሥት የበጀት ድጋፍ የሚያገኝበትን መንገድ ቀይሷል::

በዚህ ዕቅድ መሠረት ክልላዊ መንግሥቱ ከሁለት ሳምንት በፊት የከተማው ከንቲባ የነበሩትን አቶ

ጉታ ላንቾሬንና ምክትላቸውን ከሥልጣን አንስቷል:: በምትካቸው በፌዴራል ደረጃ በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ የነበሩትን አቶ በኩር ሳህሌ ሾሟል::

አቶ በኩር ሳህሌ የኦሕዴድን ማዕከላዊ ኮሚቴ ይሁንታ አግኝተው የተሾሙ ሲሆን፣ አስተዳደራቸውን ማዕከላዊ ኮሚቴው በቅርበት ይከታተለዋል ተብሏል:: የአዳማ ከንቲባ ሆነው የተሾሙት አቶ በኩር በየደረጃው ያሉ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች የሁለተኛውን የሦስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ያስጀመሩ ሲሆን፣ ግምገማው ለሁለት ሳምንት ይቆያል ተብሏል::

በግምገማው የተደረሰበት ነጥብ ከሕዝቡ ጋር ምክክር ከተደረገበት በኋላ ጥፋት አለባቸው የሚባሉ አመራሮች ዕርምጃ ሊወስድባቸው እንደሚችል ምንጮች ገልጸዋል:: ከዚህ የአመራር ለውጥ በተጨማሪ አዳማ ከተማ ከክልሉ መንግሥት የበጀት ድጋፍ እንዲደረግለት ተወስኗል::

በተለይ በቅርቡ የክልሉን የበጀት ድጋፍ ያገኛሉ

በአመራር ለውጥ የሚናጠው አዳማ የተረጋጋ አስተዳደር እንዲያገኝ ተወሰነ

ከተማውን የኦሕዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ ይከታተለዋል

ከመግለጽ በስተቀር ምንም ባለማለታቸው በሁለቱም ላይ ቅጣቱ ከብዶ ተወስኗል:: ሌሎቹ ባቀረቡት የቅጣት ማቅለያ መሠረት ቅጣቱ ቀሎ ተጥሎባቸዋል::

በሌላ በኩል በሽብርተኝነት ወንጀል ተከሳ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት የወሰነባትን የ14 ዓመታት እስራትና የ33 ሺሕ ብር ቅጣት የተቃወመችው መምህርትና ጋዜጠኛ ርዕዮተ ዓለሙ፣ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረበችው የይግባኝ አቤቱታ የተጣለባት ቅጣት ወደ አምስት ዓመታት ዝቅ ማለቱ ይታወሳል:: በድጋሚ የሕግ ስህተት መፈጸሙን በመግለጽ ለሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረበችውን አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለታህሳስ 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ትናንትና ቀጠሮ ሰጥቷል::

Page 4: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 4|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

Re-INVITATION FOR BIDTENDER NO. MBMP Pvt. Ltd. Co. 03/2005

Messebo Building Material Production PLC. (MBMP PLC) invites eligible bidders for the supply of`:

S.N Description U/M Qty Remark

Dell power edge R420 as per the attached specification

Pcs 03

Network storage as per the attached specification Pcs 01

3. Portable external hard drive(My passport) 1IB USP 3.0

Pcs 05

4. RAM for Dell power edge 2600, 1GB registered PC 2100 DDR

Pcs 04

5. Power supply for Dell power edge 2600 wattage 730W (AC) voltage 200-240VAC 50/60Hz, 5.0A

Pcs 02

6. RAM for Dell power edge 2950, 2GB 533 MHZ DDR2-533 Pc2-4200

Pcs 04

7. Hard disk for Dell power edge 2950 serial attached scsi capacity 146 Gb RPM 15K

Pcs 04

1. Tender documents can be collected from Addis Ababa Messebo Building Material Production Pvt. Ltd. Co. Liaison Office ZEFCO Building 4th Floor or Mekelle Messebo Building Material Production Plc Head office effective from the day of announcement against payment of non-refundable Birr 100.00.

2. Bidder shall be submitted valid trade license renewed for 2004 Ethiopian Calendar and VAT registered certificate.

3. All Bids should be submitted in wax-sealed and stamped envelopes on or before 14th day from the date of first announcement in the Herald News paper.

4. Messebo Building Materials production PlcAddis AbabaP.O.Box: 9620Tele: +251-11-4-663292/3, Fax: +251 114 663403ZEFCO Building 4th Floor, Addis Ababa, EthiopiaAddis Ababa, Ethiopia

Messebo Building Materials production PlcMekelleP.O.Box: 916Telephone 0348 40 06 70/0348 401336Fax: +251 -344 410863Messebo site, Mekelle Ethiopia

5. Bids will be opened on the 15th day from the date of first announcement in the Herald News paper at 10:00 AM (European time) in the presence of interested bidders or their representatives who choose to attend at the above mentioned offices.

6. Bid must be accompanied by bid bond of Birr 2% of the total price in the form of C.P.O.7. Messebo Building Material Production Plc reserves the right to reject fully or partially of

the bid.

Pax Industrial Machinery PLC ፓክስ ኢንዱስትሪያል ማሽነሪ ኃላ/የተ/ግ/ማህበር

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ (አስቸኳይ)1. የሥራ መደቡ መጠሪያ ሌዝ ማሽኒስት የሥራ ልምድ 7 ዓመትና ከዚያ በላይ ደሞዝ በስምምነትየስራ ቦታ አዲስ አበባ ብዛት ሁለት (2) 2. የሥራ መደቡ መጠሪያ ሚሊንግ ማሽኒስት የሥራ ልምድ 7 ዓመትና ከዚያ በላይ ደሞዝ በስምምነት የስራ ቦታ አዲስ አበባ ብዛት ሁለት (2) 3. የሥራ መደቡ መጠሪያ በያጅ የሥራ ልምድ 7 ዓመትና ከዛ በላይ ደሞዝ በስምምነት የሥራ ቦታ አዲስ አበባ ብዛት አንድ (1) 4. የሥራ መደቡ መጠሪያ የማሽን ረዳት የሥራ ልምድ ቢያንስ 1 ዓመት ደሞዝ በስምምነት የስራ ቦታ አዲስ አበባ ብዛት ሁለት (2)

ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የስራ ቀናት ውስጥ፡፡

ሰራተኞች በሥራቸው ታማኝና የቴክኒካል እውቀታቸውን በተግባር ማሳየት የሚችሉ፡፡

የስራ ፈተናውን አልፈው ወደ ሥራ ሲገቡ በስነ ምግባር የታነፁ መሆን አለባቸው፡፡

ለበለጠ መረጃ የስልክ ቁጥር 0114-674-511/12/14 ወይም በሞባይል ቁጥር 0911-99-06-89 መደወል የምትችሉ መሆኑን

እንገልፃለን፡፡

Vacancy AnnouncementAbay Technical and Trading Share Company seeking qualified candidates for the following Positions. No Position Educational background & experience Required1 Senior Body Man College Diploma in Metal Technology General Mechanic with 10 years experience Or Technical School Diploma with 16 years experience 1

2 Body man College Diploma in Metal Technology/ General Mechanic with 8 years experience Or Technical School Diploma with 14 years experience 2

Salary Negotiable

Terms of employment Contract

Place of work Addis Ababa Interested applicants who fulfill the above requirements can submit their non returnable copies of relevant documents with original documents and CV in person within 7 working days starting the date of the first day or this announcement, to Administration & General Service Division of the company. Address: Abay Technical & Trading S.C., Tel 251 011-5 51 54 24, P.O.Box 12602 Around Mexico Square near Genet Hotel In front of “Temama Fok”

አይ.አይ.አር ኢትዮጵያInternational Institute of Rural Reconstrucion (IIRR-Ethiopia)

አይ.አይ.አር.አር ኢትዮጵያ (IIRR-Ethiopia) መንግስታዊ ያልሆነ የልማት ድርጅት የድርጅቱን ዓመታዊ የሂሳብ ምርመራ ለማስደረግ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ የሂሳብ መርማሪ ድርጅቶችን በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ለመዳደር ፍላጐቱ ያላቸው ድርድቶች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች፡-

1. ህጋዊ የንግድ ፈቃድ እና የሙያ ማረጋገጫ ፈቃድ ያላቸው፣2. በ2005 በጀት ዓመት ፈቃዳቸውን ያደሱ፣3. የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣4. በታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ፣ እና በሂሳብ ምርመራ ሥራ ላይ በቂ የሥራ ልምድ ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡

ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ7 የሥራ ቀናት ውስጥ በምን ያህል ጊዜ ሥራውን እንደሚያጠናቅቁ እና የሥራውን መሥሪያ ዋጋ የሚገልጽ መረጃችሁን በፖስታ በማሸግ መካኒሳ ቼሻየር ፋውንዴሽን ግቢ ውስጥ በሚገኘው የድርጅቱ ቢሮ እንድታቀርቡ ይጋብዛል፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0113212994/0113212864 በመደወል መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ አድራሻ፡ መካኒሳ ወደ ቆሬ በሚወስደው መንገድ ላይ ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ጽ/ቤት ፊት ለፊት

Page 5: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 5 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ማስታ

ወቂያ

The Embassy of Canada in Addis Ababa, Ethiopia seeks a dynamic, qualified candidate for the position of:

Commercial Officer.

Reporting to the Counsellor (Political) and with the guidance of the Regional Trade Commissioner at the CanadianHigh Commission in Nairobi, the Commercial Officer supports Canadian companies and partners who wish todevelop successful commercial and investment projects in Ethiopia and Djibouti.

Closing Date for Applications: Tuesday, 24December 2012 at 17:00 local time

For more information and application details, please visit:www.ethiopia.gc.ca. Click on ‘Job Opportunities’. L’Ambassade du Canada à Addis-Abeba, Éthiopie cherche un candidatdynamique qualifié pour le poste de :

Agent commercial.

Relevant du Conseiller (Affaires politiques) et avec la direction du délégué commercial régional au commissariat du Canada à Nairobi, l’agent commercial soutient les entreprises canadiennes et les partenaires qui souhaitent développer des projets commerciaux et des investissements en Éthiopie et à Djibouti.

Date de clôture des candidatures : mardile 24 décembre 2012 à 17:00 heure locale

Renseignements disponibles en français à l’adresse suivante :www.ethiopia.gc.ca. Prière de consulter l’onglet ‘Opportunités d’emploi’.

በዮሐንስ አንበርብር

ራያ ቢራ አክሲዮን ማኅበር በትግራይ ክልል ማይጨው ከተማ ለሚያስገነባው የቢራ ፋብሪካ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ የሚሆነውን ወጪ ለመሸፈን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ይሁንታ እንደሰጠው ገለጸ::

በጥቂት ባለሀብቶችና ጊዮርጊስ ቢራን በሚጠምቀው ቢጂአይ ኢትዮጵያ 250 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል የተመሠረተው ራያ ቢራ አክሲዮን ማኅበር በትግራይ ክልል ፋብሪካውን የሚያቆምበት መሬት ተሰጥቶታል::

በመጪው እሑድ ባለአክሲዮኖችና የመንግሥት ባለሥልጣኖች በሚገኙበት ሥነ ሥርዓት ፋብሪካውን ለመትከል የመሠረት ድንጋይ እንደሚጣል ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ለማ በቀለ ለሪፖርተር ገልጸዋል::

ፋብሪካውን ገንብቶ ለጠመቃ ዝግጁ ለማድረግ ከ800 እስከ 850 ሚሊዮን ብር እንደሚፈጅ፣ ከተጠቀሰው ወጪ 250 ሚሊዮን ብር የሚሆነው በራያ ቢራ እንደሚሸፈን፣ ቀሪው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚገኝ ብድር እንደሚሟላ አስረድተዋል::

‹‹ንግድ ባንክ የብድር ይሁንታውን የሰጠን ሲሆን፣ ከእኛ የሚጠበቀው ፋብሪካውን ከሚገነባው ኩባንያ ጋር መፈራረም ብቻ ነው፤›› ሲሉ ሥራ አስኪያጁ ለሪፖርተር ገልጸዋል::

የማምረቻ መሣሪያዎችን ዲዛይን የማድረግ፣ የማምረትና ወደ አገር ውስጥ አስገብቶ የመትከል ሥራውን ለመሥራት በወጣው ጨረታ መሠረት፣ አንድ የውጭ ኩባንያ የቴክኒክና የፋይናንስ ግምገማውን እንዳለፈ፣ ነገር ግን ውል ከመገባቱ በፊት ኩባንያው በጠየቀው ክፍያ ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግ ድርድር እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፣ የኩባንያው ማንነት መናገር አልፈለጉም::

ድርድሩ ባለመጠናቀቁ ምክንያት የኩባንያውን ማንነት ከመግለጽ የተቆጠቡት አቶ ለማ፣ በዚህ ሳምንት መጨረሻ አካባቢ ከኩባንያው ጋር ውል ይፈረማል ብለው እንደሚገምቱ ግን ተናግረዋል::

ራዳር ኮንስትራክሽን የተባለ የአገር ውስጥ ኩባንያ የመሬት ዝግጅት ሥራውን ለመሥራት መመረጡንና በመጪው እሑድ ከሚካሄደው የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ ሥርዓት በኋላ የመሬት ዝግጅት፣ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታና የመሳሰሉት ሥራዎች እንደሚጀመሩ ገልጸዋል::

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ጥያቄው እንደቀረበለት አስታውቆ፣ ነገር ግን ዝርዝር መረጃ ለመስጠት የብድር ጥያቄው መፅደቅ ይኖርበታል ብሏል::

ከገጽ 3 የዞረ

ከገጽ 3 የዞረ

ራያ ቢራ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ የብድር ይሁንታ ከንግድ

ባንክ አገኘሁ አለ

ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪው የውጭ ኩባንያ ኬሚካል

ሊያቀርብ ነውፋብሪካውን ከሚገነባው የውጭ ኩባንያ ጋር ሰሞኑን ይፈራረማል በውድነህ ዘነበ

የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የአገሪቱን የጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ የኬሚካል ግብዓት ችግር ለመቅረፍ፣ ዛሬ ታህሳስ 3 ቀን 2005 ዓ.ም. ቤዝማ ዳይስና ኬሚካል ከተሰኘ የስዊዘርላንድ ኩባንያ ጋር ስምምነት ይፈጽማል::

የስዊዘርላንዱ ኩባንያ ወደ ጀሞ በሚወስደው መንገድ ከሳሙኤል ሕንፃ ጀርባ መጋዘን በመክፈት ለዘርፉ የሚሆኑ ኬሚካሎችንና የምርት ማጠናቀቂያ ግብዓቶችን በሰፊው ያቀርባል::

ኢንስቲትዩቱ ድርድር የጀመረው ቤዝማ ዳይስን ጨምሮ ከሦስት ኩባንያዎች ጋር ሲሆን፣ እነሱም ቴክስታይል ከለር የተሰኘ የስዊዘርላንድ ኩባንያና ሮዝ ቴክስታይል ከተሰኘ የቱርክ ኩባንያ ናቸው::

የኢንስቲትዩቱ አንድ ሥራ ኃላፊ እንደገለጹት፣ ሮዝ ቴክስታይል ከግዙፉ አይካ አዲስ ጋር በሽርክና ነው የሚሠራው:: ኢንስቱትዩቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከእነዚህ ሁለት ኩባንያዎች ጋር ያለውን ድርድር ለመቋጨት ስምምነት ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል::

እነዚህ ኩባንያዎች በራሳቸው ገንዘብ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪው የሚፈልጋቸውን ኬሚካሎችና የምርት ማጠናቀቂያ ግብዓቶችን ከውጭ በማምጣት በአገሪቱ ለሚገኙ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካዎች ያቀርባሉ::

የአገር ውስጥ ፋብሪካዎቹ ግዥውን የሚፈጽሙት በኢትዮጵያ ገንዘብ ሲሆን፣ የውጮቹ ኩባንያዎች ግን በብሔራዊ ባንክ በኩል ገንዘቡን ወደ ውጭ ምንዛሪ ቀይረው

ይወስዳሉ:: ከዚህ በተጨማሪም ከውጭ የገባው ዕቃ ወደ ኩባንያው መጋዘን ከገባ በኋላ ነው ፍተሻ የሚደረገው:: ይህ አሠራር ተግባራዊ የሚደረገው የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በፈጠሩት አዲስ አሠራር አማካይነት ነው::

በኢትዮጵያ የጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ ዕድገት ማነቆ ሆነው ከቆዩት ምክንያቶች አንዱ የግብዓት አቅርቦት ነው:: በዓመት ከ400 ቶን በላይ የማጠናቀቂያ ግብዓቶችና ከአሥር ሺሕ ቶን በላይ የተለያዩ ዓይነት ኬሚካሎች አገር ውስጥ ይገባሉ::

ባለሙያዎች እነዚህን ኬሚካሎችና ግብዓቶች በአገር ውስጥ የሚገኙ ሁሉም ፋብሪካዎች በተናጠል የሚያስገቧቸው በመሆኑ አሠራሩ ለማጭበርበር የተጋለጠ፣ የምርት ጥራት ችግር የተንሰራፋበት፣ የሴክተሩን ተዋናዮች የሥራ ማስኬጂያ ገንዘብ እጥረት ውስጥ የሚከት ነበር ይላሉ::

ዛሬ የሚካሄደው ስምምነትና በቀጣይነት ከሁለቱ ኩባንያዎች ጋር የሚፈጸሙ ስምምነቶች የዘርፉን ችግር እንደሚፈቱ ታምኖበታል::

የኢንስቲትዩቱ አንድ የሥራ ኃላፊ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ የሚሆኑ ግብዓቶች ፍላጎት በዓመት 20 በመቶ ዕድገት እያስመዘገበ በመሆኑ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ለእነዚሁ ግብዓቶች ግዥ ይውላል::

የውጮቹ ኩባንያዎች በተለይ ዛሬ የሚፈራረመው የስዊዘርላንዱ ኩባንያ ወደፊት ኬሚካሎችን በአገር ውስጥ የማምረት ዕቅድ እንዳለው ታውቋል::

ተብሎ በግንባር ቀደምትነት ከተቀመጡት የአዳማ ከተማ ፕሮጀክቶች መካከል የከተማውን የመጠጥ ውኃ እጥረት ለመቅረፍ የተቀመጠው ዕቅድና ከተማውን ከዓመት ዓመት እየመታ የሚገኘውን ጎርፍ በዘላቂነት ለማስወገድ የተቀመጠው ዕቅድ ይገኙበታል::

የአዳማን የመጠጥ ውኃ ችግር ለመቅረፍ የ800 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት፣ የጎርፍ ችግሩንም ለመፍታት 90 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ይደረጋሉ ተብሏል:: ከ300 ሺሕ ሕዝብ በላይ ያለው አዳማ ከተማ ከኦሮሚያ ትላልቅ ከተሞች ግንባር ቀደሙ ነው:: የክልሉ መንግሥት መቀመጫ አዲስ አበባ ቢሆንም የክልሉ ምክር ቤት (ጨፌ) የሚገኘው በአዳማ ነው:: የክልሉን ትላልቅ ኮንፈረንሶችና እንቅስቃሴዎች የሚያስተናግድበት አዳማ ከተማ የመልካም አስተዳደርና የሙስና መንሰራፋት ያለበት መሆኑ በሰፊው ይነገራል::

በአመራር ለውጥ...

አላስፈላጊ ውዥንብር ውስጥ ይከታል በሚል ተሰግቶ መሆኑን የሚናገሩ አሉ:: ጋዜጣው ከዚያን ጊዜ አንስቶ ተዘግቶ የቆየ ቢሆንም፣ ጋዜጠኛ ተመስገን በማኔጂንግ ኤዲተርነት ‹‹አዲስ ታይምስ›› በሚባል መጽሔት ላይ እየሠራ ይገኛል::

ተቋርጦ የነበረው...ማስተካከያ

ኅዳር 2 ቀን 2005 ታትሞ በወጣው ጋዜጣ ከ“300 በላይ ዜጎች ከሶማሊያ እሥር ቤቶች ያልተሻለ ሕይወት እየኖሩ ነው” በሚል ርዕስ በቀረበው ዜና በኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ልዑክ ኃላፊ ሚስተር ፒተር ጂ ስቶከር ባደረጉት ንግግር “ለ11 ዓመታት በሶማሊያ እሥር ቤቶች በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን በደል እ.ኤ.አ. በ1988 ዓ.ም. ለመመርመር ኃላፊነት ስለነበረኝ ወደ ሶማሊያ ሄጄ መዛግብትን አገላብጫለሁ፡፡ መዛግብቱ እንደሚያስረዱት የዓለም ቀይ መስቀል ኮሚቴ በዓመት ሁለት ጊዜ ከጄኔቫ ልዑካን እየላከ የሶማሊያ መንግሥት ለእሥረኞች ዕርዳታ ለመስጠት በሩን እንዲከፍት ለመደራደር ይጠይቅ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የሶማሊያ መንግሥት በሩን ዘጋው፤” ብለዋል የተባለው በስህተት የገባ ነው፡፡ ስለሆነም “የጦር ምርኮኞቹ ዕውቅና እንዲያገኙና በማኅበረሰቡ ውስጥ ተገቢው ሥፍራ እንዲሰጣቸው የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ማኅበሩ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ ቦታ በመስጠታችን ኩራት ይሰማናል፤” ብለዋል በሚለው እንዲስተካከል ከይቅርታ ጋር እንጠይቃለን፡፡

Page 6: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 6|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

የ ጨ ረ ታ ማ ስ ታ ወ ቂ ያ ብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት/ኢትዮጵያ/ አ.ማ. የኮስት ፖሊሲና ፕሮጀክት ማንዋል የሚያዘጋጁ ኮንሰልታንቶች በጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መሥፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን ለወድድር ይጋብዛል፡፡

1. ተጫራቾች ለ2005 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በሚመለከተው መ/ቤት የተመዘገቡበትን የአማካሪነት የምስክር ወረቀት እንዲሁም የቫት ተመዝጋቢ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ኦሪጅናልና ፎቶ ኮፒ የጨረታ ሠነድ ለመግዛት ሲመጡ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

2. ተጫራቾች የጨረታውን ሠነድ የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ/ በመክፈል የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በድርጅቱ የሀገር ዋስጥ ግዥ ቢሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡

3. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ /ቢድ ቦንድ/ በሚያቀርበው ጠቅላላ ዋጋ ላይ 1% በባንክ በተመሰከረ ቼክ (ሲፒኦ) ወይም የባንክ ጋራንቲ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

4. ተጫራቾች ከላይ የተገለፀውን ማንዋል ለማከናወን የሚጠይቁትን ዋጋና ሌሎች ዝርዝር ቴክኒካል ሁኔታዎችን በሁለት በተለያዩ የታሸጉ ኢንቨሎፖች እስከ ታህሳስ 25 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ለድርጅቱ መዝገብ ቤት ማስገባት አለባቸው፡፡

5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ታህሳስ 25 ቀን 2005 ዓ.ም 8፡45 ሰዓት በዋናው መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ተጫራቾች በተገኙበት ይከፈታል፡፡

6. አሸናፊ ተጫራቾች የጠቅላላ ዋጋ 10% የመልካም ሥራ አፈፃፀም (performance Bond) ያስይዛል፡፡

7. ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ብሔራዊ የትምባሆ ድርጅት/ኢትዮ/አ.ማ

ስልክ ቁጥር 011-551-00-44 የውስጥ መስመር 254

011-8966120

ማስታ

ወቂያ

VACANCY ANNOUNCEMENTTOTAL ETHIOPIA S.C. would like to announce the following vacant position for candidates who fulfill the requirements listed below:-

1. Position: AVIATION CREW CHIEF Educational Background & Experience: Diploma from accredited school/college Experience Skills Required: A minimum of four years hands on experience in driving trucks with trailer. 5th grade driving license. Performs fuel quality, refueller, aviation

equipment inspection and in to plane operation (drive refueller with trailer). Good team work skill and ability to work in team environment

Ability to work under tight time schedule and tense working environment

Good interpersonal skills to manage internal and external interfaces.

Strong customer awareness and focus. Good safety awareness

Work Place Addis Ababa Bole Aviation Salary As per the Company Scale

Interested applicants are invited to submit their updated CV And photocopies of relevant documents to Human Resource & Public Affairs Department at Head Office Debrezeit Road or send through post office within 10 days of this advertisement.

Human Resource & Public Affairs Department.Tel. NO. 251 11 465 11 25 Fax: 251 11 465 10 39 P.O.Box 1462

TOTAL ETHIOPIA

በየማነ ናግሽ

አንድ በ20ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ ወጣት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ‹‹ቶክ ቱ አልጀዚራ›› ከሚለው የአልጄዚራ የቴሌቪዥን ጣቢያ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በድረ ገጽ ለማግኘት እየታገለ ነው:: አልጄዚራ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲዘጉ ከተደረጉ ድረ ገጾች መካከል ነውና አልቻለም:: ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃለ ምልልስ የሰጡት ለጋዜጠኞቹ ብለው ነው? ወይስ በአገራቸው ሕዝብ እንዲነበብ እንዳይታይ ከማይፈቀደው ሚዲያ ጋር መነጋገራቸው ምን ይሉታል?›› እያለ ከጓደኞቹ ጋር በማጉረምረም ከአንድ ኢንተርኔት ካፌ ሲወጣ አየሁት::

እውነት ነው፤ የአልጄዚራ ቴሌቪዥን ጣቢያ ባይዘጋም ዘመኑ ባመጣው የኢንተርኔት ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ ማዳመጥ ወይም ደግሞ ማንበብ ለሚፈልግ ሰው ግን አይቻልም::

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የተለያዩ አገራዊና አካባቢያዊ ጉዳዮችን አስመልክተው የ25 ደቂቃ ቃለ ምልልስ ያደረጉበት ከኳታር (ዶሃ) የሚሠራጨው የአልጄዚራ የቴሌቪዥን ጣቢያ ድረ ገጽ ተዘግቷል:: ቪኦኤ፣ ናዝሬት፣ ዓባይ፣ ኢትዮ ሚድያ፣ መርካቶና ሌሎች በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ከፍተኛ ፖለቲካዊ ትችቶችን የሚያስተናግዱ ድረ ገጾችም እንደዚሁ ተዘግተዋል:: ኢትዮጵያ ሚዲያዎችን በማፈን፣ ጋዜጠኞችን በማሰርና በማዋከብ ግንባር ቀደም ከሆኑ አገሮች ስሟ እየተጠራ ሲሆን፣ በተለይ ግን ድረ ገጾችን ‹‹ጃም›› በማድረግ በቅርብ ጊዜያት ቀዳሚ ሳትሆን እንደማትቀር ብዙዎች ይስማማሉ::

ያም ሆነ ይህ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ከአልጄዚራ ጋዜጠኛዋ ዥ ዱተን ጋር

ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር ስለተፈጠረው ቀውስ፣ ዕርዳታ ለፖለቲካ ጥቅም ፍጆታ ስለመዋሉ፣ የመሬት ወረራ፣ በቅርቡ ስለተደረገው የሥልጣን ሽግግርና የዓባይን ግድብ በተመለከተ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ፈገግ እያሉ ምላሽ ሰጥተዋል:: በእነዚህ ጉዳዮች ላይ በጋዜጠኛዋ ጥያቄዎች ሲቀርቡላቸው፣ በተለይ ደግሞ ግብፅንና ሱዳንን በተመለከተ ጋዜጠኛዋ ያቀረበችው ጥያቄ ከመረጃ እጥረት የተነሳ መሆኑን እያዋዙ ዘና ብለው ሲናገሩ፣ ከዚህ በፊት ለአገር ውስጥ ከሰጡዋቸው ማብራሪያዎች ብዙም ያልተለዩ ነበሩ::

አዲሱ ነገር ኤርትራን በተመለከተ ነበር:: በሁለቱ አገሮች መካከል ስለሚደረገው የእግር ኳስ ጨዋታ ተጀምሮ በአገሮቹ መካከል ስላለው ግንኙነት ‹‹ስፖርትንና ፖለቲካን›› በመቀላቀል ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጡት ምላሽ ይገኝበታል:: ‹‹ኢትዮጵያና ኤርትራ በአፍሪካ ሻምፒዮንሺፕ የሚያደርጉት ጨዋታ በገለልተኛ ሜዳ እንዲካሄድ ጠይቃችኋል›› በማለት በተነሳ ጉዳይ፣ የሁለቱን አገሮች ግንኙነት ያባብስ ይሆን ወይ በማለት ጋዜጠኛዋ ጠየቀቻቸው:: ‹‹እግር ኳስ ነው ያልሽኝ?›› እና ‹‹የትኛዋ አገር?›› በሚል ማጣጣል በሚመስል በጀመሩት ንግግር ስለተነሳው ጉዳይ ምንም መረጃ እንደሌላቸው ነበር የገለጹት:: ቀጠል አድርገው ግን፣ ‹‹ሆኖም ግን አስመራ ድረስ በመሄድ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ለመነጋገር ትፈልጋለህ ወይ የሚል ጥያቄ ብታቀርቢልኝ?›› በማለት ራሳቸው ቀድመው ላነሱት ጥያቄ ‹‹ምላሼ አዎ ነው›› ብለዋል::

እሳቸው የተኩዋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊም ከሃምሳ ጊዜ በላይ እንነጋገር የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውን አስታውሰው፣

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ግን በግትር አቋማቸው ምክንያት ተገቢ ምላሽ እንኳን አለመስጠታቸውን ነበር የተናገሩት:: የመደራደር ጉዳይ ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግሥት የመቼም ጊዜ አቋም መሆኑ የገለጹት ግን፣ ‹‹አካባቢያዊ ውህደት መፍጠር›› የሚል አዲስ አስተሳሰብ ሊሰጥ የሚችል አስተያየት ጣል አድርገዋል:: የኃይለ ማርያም የአስመራ መንገድ ከመለስ የተለየ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል::

መለስና ኢሳይያስ

ባለፈው ዓመት ከዋናዋ ሱዳን ተገንጥላ አዲስ አገር ሆኖ ከመጣችው ደቡብ ሱዳን ቀደም ብላ ወደ የዓለም አገሮችን የተቀላቀለች ኤርትራ ነበረች:: ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂም የኤርትራውያን የነፃነት አባት ተደርገው ይቆጠሩ ነበር:: በአንፃሩ ደግሞ የቀድሞ የትግል አጋራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ፣ አገርን አስገንጥለዋል በሚል በተቃዋማዎቻቸው የሚሰነዘርባቸው ተቃውሞ የፖለቲካ ኪሳራ አድርሶባቸዋል:: ሁለቱም ታጋዮች ደርግን ከመጣልና የኤርትራ ነፃነትን ከመደገፍ ውጭ በምንም ዓይነት ፖለቲካዊ እሳቤዎችና ወታደራዊ ስልቶች የሚስማሙ አልነበሩም:: እንደ ጓዶች ከሚቆጠሩ ይልቅ እንደ ባላንጣዎች የሚታዩ ናቸው::

ደርግን ለመጣል ሙሉ ስምምነት ነበራቸው ቢባልም፣ አንዱ ከሌላው እየተደበቀ ከፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ጋር በመነጋገር ችግራቸውን ለመፍታት የተደረጉ ሙከራዎች እንደነበሩ ይነገራል:: ሁለቱም መሪዎች ግን አንድ ስለመሆን ወይም ደግሞ የኤርትራን መገንጠል ለማስቆም ያደረጉት አንዳች ጥረት ለመኖሩ መረጃ አልተገኘም:: ሁለቱም ባላንጣዎች አንድን

የኃይለ ማርያም የአስመራ መንገድ ከመለስ ይለይ ይሆን?

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ

Page 7: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 7 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ማስታ

ወቂያ

Sustainable Natural Resources Management Association

(SUNARMA)

Call for Audit ServiceSustainable Natural Resource Management Association (SUNARMA) is a national NGO established in the year 2000 and registered as Ethiopian Resident Charities, bearing Certificate No. 0296.

SUNARMA would like to invite eligible audit firms to conduct its accounts for the 2012 fiscal year, (1st January to 31st December).

Accordingly, interested professional and authorized audit firms are invited to submit the following documents to SUNARMA’S Head Office in wax-sealed envelope, stating their address to participate in the bid for the annual audit within ten days of this announcement and the bid will be opened on the tenth day at 10:30 A.M. at the organization Head Office Conference Room in the presence of Bidders or their legal representatives. The bidders should include the following requirements:

1. Renewed license;2. Evidence showing that the firm has paid current year tax;3. Tax identification number;4. Technical and financial proposal including time frame to accomplish the task.

Note: - SUNARMA reserves the right to accept or reject any or all bids at its own discretion.

For any additional information, please contact SUNARMA Head Office.

Address:- Gurd Shola, Abenezer Building, 3rd floorP.O.Box: 6942, Addis Ababa, Ethiopia

Tel: +251 11 646 42 13/+251 11 651 46 92Email:[email protected]

Invitation For BidNo. EAC/ Bid-05/04-05

Ethio Agri-CEFT PLC is looking for potential bidders for drilling of borehole, supply & installation of submersible pump and water tankers at the premise of Tea processing & packing factory, Addis Ababa.

Interested bidders are invited to submit their offer within 15 consecutive working days from the date of the announcement on the Newspaper.

Bid documents shall be obtained from Ethio Agri-CEFT PLC’s Head Office, Yeka Sub-city, Haile G/Selasie Street, WARYT Building 4th floor, Commercial Department during working hours upon payment of non-refundable fee of Birr 100.00 (one hundred) only.

All Bids must be accompanied by a bid security of 2% of the total bid amount in a form of Bank Guarantee.

Offers shall be submitted in wax-sealed envelope.Bids will be closed on the 15th day at 5:00 pm (local time) and

be opened on the next working day at 10:00 am (local time) in the presence of the bidders or their legal representatives, at the company’s meeting room.

Ethio Agri CEFT PLC reserves the right to reject all or part of this

bid.

ETHIO AGRI-CEFT PLC

Tel: 011-6621030, 011-6637780, 011-6637781

አገር በጋራ መምራት የሚችሉ አልነበረም::

የሁለቱም መሪዎች ባላንጣነት አንዱ የሌላው አለቃ ሆኖ ለመሥራት የሚያስችላቸው አልነበረም:: ሁለቱም የበላይ አለቃ መሆን ነበረባቸው:: በዚህም ሁለት አገሮች መፈጠር ነበረባቸው:: ይህ በአብዛኛው ለሁለቱም መሪዎች ቅርበት የነበራቸው ውስጥ አዋቂ ፖለቲከኞች የሚያቀነቅኑት ነው::

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የኤርትራን ነፃነት በተመለከተ ገና ከጠዋቱ ከትጥቅ ትግል ጊዜ ጀምረው የሚያምኑበት የፀና አቋማቸው ቢሆንም፣ ኤርትራ በኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ሥር ነበረች የሚለው ፖለቲካዊ ትንታኔያቸው እጅግ የበዛ ነቀፌታ እንዲሰነዘርባቸው ምክንያት ሆኗል:: ሆኖም ከውጭም ከውስጥም የሚደመጠውን ነቀፌታ የሚቀበሉ አልነበሩም::

ውኃ ቅዳ ውኃ መልስ

ኤርትራውያን እንደ ሌሎቹ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የደረሰባቸው ጭቆና ለአንዴና ለመጨረሻ ለመገላገል ነበር ለ30 ዓመታት ያህል ጦርነት ማካሄዳቸውን የሚናገሩት:: የታላቋ ኢትዮጵያ ለሁለት መሰንጠቅ ግን ከመለያየቱ ጀምሮ ጤነኛ አልነበረምና የተጠበቀውን ያህል ሰላም አላስገኘም:: የሁለቱም አገሮች ዳር ድንበር በውል ሳይካለል፣ በኢትዮጵያ የነበሩ የኤርትራ ተወላጆች የዜግነት ጥያቄ ግልጽ መፍትሔ ሳይደረግበት በይደር ነበር የቆየው::

ሁለቱም መሪዎች መንግሥታቸውን በምሥራቅ አፍሪካ ውስጥ ከፍተኛ ተፅዕኖ ለማሳደር በሚያደርጉት ግስጋሴ ተፎካካሪነታቸው እየጨመረ የመጣው የኤርትራ መንግሥት ኢኮኖሚያዊ ብዝበዛ በተጀመረበት ወቅት ነበር:: በመጨረሻ ግን የሁለቱም አገሮች ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት መልኩን እየቀየረ በመምጣቱ አንዱ በሌላው ላይ ማሴር ጀምረው ነበር ይባላልም:: ይኼ ሁሉ የፈነዳው ግን በይደር በቆየው የድንበር ግጭት ወቅት ነበር:: የድንበር ግዛት የይገባኛል ጥያቄ ዋነኛ ማዕከል ሆኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስሟ ሲጠቀስ በነበረው ባድመ ላይ በተደረገው ውጊያ ከሁለቱም አገሮች ከ70 ሺሕ በላይ ወጣቶች በጦርነቱ ተሰው ከዚያም ጉዳዩን በበላይነት ይዞት የቆየው ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ሁለቱንም አገሮች ወደ ሌላ ዘር ጦርነት የሚከት

ፍርድ በመስጠት እነሆ “ሰላምና ጦርነት አልባ” እንዲሆን አደረገው:: በአካባቢው ሰፍኖ የቆየው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ሰላም አስከባሪ ኃይል ደግሞ ለቆ በመውጣቱ ዛሬ ወይም ነገ ይፈነዳል የተባለው ጦርነት ዋል አደር እያለ እዚህ ደርሷል::

የመለስ መንገድ

ጦርነቱ በኢትዮጵያ ወታደራዊ የበላይነት መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ ጠረጴዛ ዙርያ ድርድር ለመምጣት የቸኮሉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ፣ በዓለም አቀፉ የኢትዮ ኤርትራ ድንበር ኮሚሽን ውሳኔ ደስተኛ ነበሩ:: ኢትዮጵያም የምትቀበለው አልሆነም:: የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ሰላም አላመጣም:: ለችግሩም ምንም እልባት አላስገኘም:: ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ እንደ አማራጭ ባቀረቡት ባለአምስት ነጥብ የእንደራደርና የሰላም ሐሳብ ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ በሚገርም ሁኔታ ከጎናቸው ማሰለፍ ችለው ነበር::

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ግን በዚሁ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የፖለቲካ አካሄድ በመበለጣቸው የባድመን ግዛት ብቻ ሳይሆን፣ አሜሪካን ጨምሮ ዋነኛ ወዳጆቻቸውንም ያስቀረባቸው ነበር:: በዘ ሔግ ፍርድ ቤት ውሳኔ የተቆጣችው ኢትዮጵያም ወታደራዊ የበላይነቷ ወዳጅ አላሳጣትም:: በአፍሪካ ቀንድ የሽብርተኝነት ሰለባ የሆኑት ምዕራባዊያን ከሁለቱም ባላንጣዎች አንዱን መምረጥ ነበረባቸው:: የዓለም ፖለቲካ ባህል ነውና ደካማውን ለመምረጥ አልተገደዱም:: የጠቅላይ ሚኒስትር መለስን የሰላም ሐሳብ ተቀብለው ኤርትራ እንድትቀበል ጫና መፍጠር ጀመሩ:: በዚህም የተነሳ ከጎረቤት አገሮች ጋር እንደ እብድ ውሻ ሲናከስ የነበረው የኤርትራ መንግሥት ከራሱ ሕዝብና ከዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ጋር መጣላቱን ተያያዘው::

በወቅቱ በሁለቱ አገሮች መሪዎች መካከል ከነበረው የቃላት ጦርነት ልውውጥ በተጨማሪ፣ የኤርትራ መንግሥት የኢትዮጵያ አማፂ ኃይሎችን በመደገፍና በማስታጠቅ የተለያዩ የሽብር ተግባሮች መፈጸምን እንደ አንድ አማራጭ ይዞ ነበር:: ቀጥሎም፣ በሶማሊያ የተቋቋመውን የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ኅብረት በመደገፍ፣ በኢትዮጵያ ላይ ጅሃድ እንዲያውጅ በማድረግ በፈጸመው የእጅ አዙር ጦርነትም ተሸንፏል::

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ በአንድ ወቅት ፓርላማ ቀርበው በሰጡት ማብራርያ፣ ከኤርትራ ጋር ጦርነት ከተጀመረ የማይመለሱበትና እስከ መጨረሻ እንደሚሆን ዝተው ነበር:: በቀጥታ ወታደራዊ ጥቃት ሳይፈጽም፣ የተለያዩ የእጅ አዙር ጥቃቶችን ማስፈጸም የተያያዘው የኤርትራ መንግሥት ግን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጭምር በተረጋገጠው በአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ወቅት አዲስ አበባ ውስጥ ሊፈጽመው ተዘጋጅቶ በከሸፈበት ሙከራ ማዕቀብ እንዲጣልበት ምክንያት ሆኗል:: በአጠቃላይ ከዓለም የዲፕሎማሲ መነጠል (Isolation) የገጠመው ሲሆን፣ በአገር ውስጥ የሚያካሂደው ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አፈና ታክሎበት፣ በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ከፍተኛ ትችትና ነቀፌታ ሲሰነዘርበት ቆይቷል::

አብዛኛዎቹን ኢትዮጵያዊያን እንቅልፍ ስለሚነሳው የባህር ወደብ ጉዳይ ማንሳት ባይቻልም፣ የኤርትራ መንግሥትና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅ ግን በአካባቢውም፣ በአኅጉርም፣ በዓለም አቀፍ መድረክም ከፖለቲካ ጨዋታ ውጪ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሎ ነበር:: በወቅቱ የቀረበው የሰላም ሐሳብ የዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ቀልብ ለመሳብ እንጂ ከልብ የመነጨ አልነበረም ይላሉ የፖለቲካ ተንታኞች:: ይኼ ሁሉ የፖለቲካ ጨዋታ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ መንገድ እንደነበር አይዘነጋም::

የኃይለ ማርያም መንገድ

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ በሕይወት ሳሉ ኤርትራን ከዓለም ዲፕሎማሲ መነጠል ቢቻላቸውም፣ ከኤርትራ በኩል በቀጥታና በተዘዋዋሪ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ግን የሚያስቆም አልነበረም:: ከሁለት ዓመታት በፊት በአፋር አካባቢ በቱሪስቶች ላይ በተፈጸመው የማገትና የግድያ ተግባር የተማረረው የኢትዮጵያ መንግሥት በኤርትራ ላይ የፖሊሲ ለውጥ ማድረጉን አበሰረ:: ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያምም በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተደረገ ስለተባለው ለውጥ ሰፊ ማብራርያ ሰጥተው ነበር:: በተለይ ተመጣጣኝ ወታደራዊ ዕርምጃ የመውሰድ ፖሊሲን በተመለከተ:: የተደረገው የፖሊሲ ለውጥም በተወሰነ ደረጃ በተግባር የታጀበ ነበር:: የኢትዮጵያ ወታደሮች ኤርትራ ግዛት ውስጥ በመዝለቅ ወታደራዊ ጥቃት ፈጽመው መውጣት ችለዋል:: በባድመ

አካባቢ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ በተወሰደው የማገት ዕርምጃ ምክንያትም ተጨማሪ ወታደራዊ ዕርምጃ ለመውሰድ የኢትዮጵያ መንግሥት ተገዶ ነበር::

ሰሞኑን ከአልጄዚራ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ግን፣ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር መነጋገር እንደሚፈልጉ ተናግረዋል:: ሥልጣን ከጨበጡ ሦስት ወራት ያልሞላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ “የጠቅላይ ሚኒስትር መለስን ራዕይ አስፈጽማለሁ፤” በማለታቸው ከአንዳንዶቹ ትችት ቢጤ ቢቀርብባቸውም፣ አሁን በኤርትራ ጉዳይ ላይ በሰጡት አስተያየት ግን ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ራዕይም ወጣ ያለ ይመስላል እየተባለላቸው ነው:: “ወደ አስመራ በመሄድ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር ትቀመጣለህ ወይ? ትነጋገራለህ ወይ? ብለሽ ከጠየቅሽኝ መልሴ አዎ ነው፤” ሲሉ ተደምጧል::

“ለእኛ ዋነኛ ጉዳያችን ድህነትን መዋጋት ነው:: እንዲሁም ደግሞ አካባቢያዊ ውህደት መፍጠር:: ሁለታችን ይህንን ማድረግ ከቻልን ምርታማ እንሆናለን፤” በማለትም አክለው ተናግረዋል:: ድህነትን በተመለከተ በአብዛኛው የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም አስተያየት አሁንም በመለስ አቋሞች ላይ ያጠነጠነ ቢመስልም፣ “ውህደት መፍጠር ከቻልን” የሚለው ግን አዲስ ‹‹መላ›› ይመስላል:: ‹‹ውህደት መፍጠር›› የሚለው ንግግር አቶ መለስ አንስተውት የማያውቁት ርዕሰ ጉዳይ ሲሆን፣ አንድ አዲስ ምዕራፍ አመላካች ሊሆን ይችላል የሚል ትንታኔ እየተሰጠበት ነው:: ምናልባትም ሐሳባቸው በአቻቸው በፕሬዚዳንት ኢሳያስ ተቀባይነት የሚያገኝ ከሆነ፣ ከአሥር ዓመታት በላይ የዘለቀው የሁለቱም አገሮች “ሰላምና ጦርነት አልባው” ግንኙነት መልኩን በመቀየር አዲስ ታሪክ ያስመዘገባል እየተባለ ነው:: አገራቸው ውስጥ ባለው ሁኔታ ተቀባይነት ያጡትን ፕሬዚዳንት ኢሳያስም ምናልባት ከገቡበት ጥልቅ አዘቅት ውስጥ ሊያወጣቸው ይችላል:: አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያምም፣ በኢትዮጵያዊያን ዘንድ የበለጠ ተቀባይነት ለማግኘት ሊጠቀሙበት የሚገባ የፖለቲካ ካርድ ሊሆን እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች ያስረዳሉ::

Page 8: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 8|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

በብርሃኑ ፈቃደ

ሶፍትዌር በመፍጠር እንዲሁም የንግድ ትልመ ሐሳብ ወይም የቢዝነስ ፕላን በማዘጋጀት ዘርፎች ከተወዳደሩ ወጣቶች ውስጥ በሁለቱም መወዳዳርያ መስኮች ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ለወጡ ወጣቶች የገንዘብና የላፕቶፕ ኮምፒውተር ሽልማቶችን የሰጠው የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ የልህቀት ማዕከል (ICT Center of Excellence) ነው::

ከትናንት በስቲያ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ አዳራሽ ሁለተኛው የአይሲቲ ንግድ ሥራ ፈጠራ ዓመታዊ ጉባዔ ሲካሄድ ለቴክኖሎጂ ፈጣሪዎቹ ከመቶ ሺሕ ብር ጀምሮ ከፍተኛ ደረጃ ያላቸውን የላፕቶፕ ኮምፒውተሮች የሸለመው የልቀት ማዕከሉ፣ ለፈጣሪዎቹ የገበያ ዕድል በማመቻቸትም ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው አስታውቋል::

አንደኛ በመውጣት ላዘጋጀው የአይሲቲ ሶፍትዌር የላፕቶፕ ኮምፒውተር ከነማተሚያው ተሸላሚ የሆነው የቢጂአይ ባልደረባው ሄኖክ አድነው፣ ዜኖ ብሎ የሰየመው ሶፍትዌር ለአልሙኒየም በሮችና መስኮቶች የዲዛይንና ኦፕቲማይዜሽን ሥራ የሚሠራ ነው:: ሶፍትዌሩ የዲዛይንን ሥራ ከማቅለሉም ባሻገር ብክነትን እንሚያድን ሄኖክ በገለጻው አስረድቷል:: ለዚህ ሥራው ከፍተኛ ደረጃ ያለው ላፕቶፕ ኮምፒውተር ሽልማት በማግኘት አንደኛ ወጥቷል::

ረጋን ዳንኤልና ጓደኞቹ ፀረ ኮምፒውተር ቫይረስ በመፍጠር ሁለተኛው ደረጃ ሲያገኙ፣ ሀሁ የሕፃናት መማርያና መጫወቻ ሶፍትዌር የሠሩት፣ ፈርሃን ከማልና ጓደኞቹም የላፕቶፕ ሽልማት አግኝተዋል::

የቢዝነስ ፕላን በማዘጋት ሐሳባቸውን ያቀረቡት አሳይ ንጉሤና ጓደኞቹ ላቀረቡት

ፕሮጀክት የ100 ሺሕ ብር ሽልማት በማግኘት አንደኛ ወጥተዋል:: በቱሪዝም መስክ ሐረርና ዙርያ ገበዋ ላይ ስለሚገኙ የመስህብ ሥፍራዎች የተሟላ የቱሪስት መረጃ ለመስጠት የሚያስችል የኢንፎርሜሽን ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል ዕቅድ የቀረበበት ሥራ መሆኑን ፈጣሪዎቹ አስታውቀዋል:: ስለበረራ መረጃዎች በተቀላጠፈና ጊዜ በሚቆጥብ መንገድ ለተጠቃሚ ማቅረብ እንደሚቻል ነድፎ ያቀረበው አቤኔዘር ገርማንድ ሲሆን፣ የ75 ሺሕ ብር ሽልማት አግኝቶበታል:: ሦስተኛ የወጣው ናትናኤል ጎሳዬ ደግሞ በአዲስ

አበባ የሚካሄዱ ክንውኖችን የሚካሄዱበትን አካባቢ ሳይቀር የሚጠቁምና ምንም ዝግጅቶች እንደሚካሄዱ መረጃ የሚሰጥ ዌብሳይት ፈጥሯል:: ይህ ዌብሳይት አዲስ ኤቨንትስ በሚል የንግድ ስያሜ ወደፊት ገበያ ላይ እንደሚወጣም አስታውቋል:: ለዚህ ሥራው ግን የ50 ሺሕ ብር ሽልማት አግኝቶበታል::

የአይሲቲ ልቀት ማዕከል ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ቴዎድሮስ መብራቱ በተለይ የቢዝነስ ፕላን አቅርበው ተሸላሚ የሆኑ ወጣቶች ገንዘቡ በጥሬ እንደማይሰጣቸው አስታውቀዋል:: ባንክ በስማቸው ይቀመጥና፣ በብድር ወስደው በዕቅዳቸው መሠረት ለሚያከናውኑት ተግባራዊ ሥራ እየተተመነ ገንዘቡ ይለቀቅላቸዋል ያሉት አቶ ቴዎድሮስ፣ ወደፊት ደግሞ እንዲህ ያለውን ሽልማት በተለያዩ መስኮች ላይ ተሰማርተው ለሚገኙ ለመስጠት እንደታሰበ አስታውቀዋል:: ለአብነት በሕክምና ዘርፍ ላይ አይሲቲን በተለየ ደረጃ ለአገልግሎት ያበቁና ሌሎችም ይህንን ሽልማት ሊያገኙ እንደሚችሉ ይጠበቃል::

በየዓመቱ እንዲህ የሚቀጥለው ይህ ክንውን በኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ፣ ሥልጠና በመስጠት እንዲሁም በማማከር ሥራዎች ድጋፍ እንዲሰጥ በመገናኛና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተቋቁሞ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኩል ሥራው የሚካሄደው የአይሲቲ ልቀት ማዕከል፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችንና ሐሳቦችን ለሚያመነጩ ወጣቶች የገበያ ዕድል በመፍጠር፣ ቴክኖሎጂዎቻቸው በኢትዮጵያም ሆነ በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ዘንድ ተቀባይነት አግኝተው እንዲሠራባቸው ዕድል ለመስጠት እንደሚፈልግ ሚኒስቴሩ አስታውቋል::

በሌላ በኩል በጉባዔው ላይ ከተገኙ ኩባንዎች

መካከል ኤምቲኤን ከሁለት ሳምንት በፊት የኢንቨስትመንት ፈቃዱን በመውሰድ ሥራ የጀመረ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ቢሮ ከከፈተም ሰነባብቷል:: ኤምቲኤን በአፍሪካ የሞባይል አገልግሎት ላይ ታዋቂ ከመሆን አልፎ በ24 አገሮች ውስጥ አገልግሎቱን እየሰጠ ሲገኝ፣ ከዚያም ባሻገር በሶርያ፣ በየመን፣ በኢራንና በአፍጋኒስታን ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል:: አትዮጵያ ውስጥ በተዘረጋው የቴሌኮም መሠረተ ልማት ላይ ተጨማሪ አገልግሎት እንዲሰጡ ለግል ኩባንያዎች መፈቀዱን ተከትሎ ወደገበያው የገባው ኤምቲኤን፣ በተለይ በሞባይል አገልግሎት ዘርፍ፣ የጽሑፍ መልዕክቶችን ቀዳሚ በማድረግ በመጪው ጥር ወር መጀመርያ ሥራ እንደሚጀምር የኩባንያው የሚዲያ ጉዳዮች ተወካይ አቶ ሀዲስ አለማየሁ ለሪፖርተር አስታውቀዋል:: ኩባንያው ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ድጋፍ ለመስጠትም ስምምነት ማድረጉ ይታወሳል::

በአፍሪካ ቀዳሚ እንደሆነ የሚነገርለትና 14 ሺሕ ኪሎ ሜትር የፋይበር ኦፕቲክ ኔትዎርክ መስመር ቢዘረጋም፣ አገልግሎቱ ላይ የጥራት ችግርና መቆራረጥ ለቅረፍ እስካሁን አልተቻለም:: የተዘረጋው ኔትዎርክ በአፍሪካ ቀዳሚነቱ ሲነገር ደቡብ አፍሪካ ትልቁን የፋይበር ኦፕቲክስ የዘረጋችው ወደ ዘጠኝ ሺሕ ኪሎ ሜትር ገደማ በመሆኑ ኢትዮጵያን የምትከተል እንድትሆን አድርጓታል::

ኤችፒና አይቢኤም ኩባንያዎችም ስላሏቸው ቴክኖሎጂዎችና ስለአግልግሎቶቻቸው ጽሑፎችን አቅርበዋል:: አፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽንም ለአፍሪካ ከሚሰጣቸው ድጋፎች ውስጥ ለወጣቶች የሚሰጠውን የአይሲቲ ውድድርና ሽልማት በተመለከተ ገለጻ ሰጥቷል::

የአይሲቲ ልቀት ማዕከል ለቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች ሽልማት አበረከተ

ሄኖክ አድነው

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/ታምራት ጌ

ታቸው

በብርሃኑ ፈቃደ

አዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ከኔዘርላድንስ ኪንግደም ኤምባሲ ጋር በመሆን ለሦስት ዓመታት የሚቆይ የሦስት ሚሊዮን ዩሮ ፕሮጀክት ይፋ አደረገ፡፡ ፕሮጀክቱ በአምስት የተለያዩ ዘርፎች የተከፋፈለ ሲሆን በግብርና ንግድ ሥራ መሰማራት ለሚፈልጉና ድጋፍ ማግኘት ለሚሹ ኩባንያዎች ድጋፍ እንደሚሰጥ ሲገለጽ፣ ከመጪው ጥር ወር ጀምሮ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ይጠበቃል፡፡

‹‹እግዚአብሔር ምድርን ፈጠረ ደቾችም ምድርን ሠሯት፤›› የሚለውን የቆየና ስለኔዘርላንዶች የሚነገረውን አባባል በንግግራቸው ውስጥ ጣል ያደረጉት የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው ዘገየ ናቸው፡፡ አቶ አያሌው እንዳሉት፣ አንድ አሥረኛው ኢትዮጵያዊ የግብርና ሥራ ላይ ቢበረታ ኢትዮጵያንና ከዚያም ላለፈው ሕዝብ የምግብ መገኛ መሆን ይችላል፡፡ የግብርና እምቅ ሀብት ቢኖርም ዕውቀቱ እንደልብ ባለመኖሩ ምክንያት የደቾች ድጋፍ ለአዲስ ሥራ ፈጣሪዎች ዕድል እንደሚሰጥ አስታውቀዋል፡፡ የደቾች የዕውቀት ድጋፍ ገንዘብ ታክሎበት መምጣቱ ‹‹እንደተፈጠረ ባለው የእግዜር መሬት›› ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ተናግረዋል፡፡

የኔዘርላንድስ ኪንግደም አምባሳደር ሃንስ ብላንክንበርግ ሲናገሩ፣ የግብርና ውጤቶችን ለማቀነባበር የሚያስችለው አዲሱ የግብርና ንግድ ሥራ ከማቀላጠፍ ባሻገር በኢትዮጵያና በኔዘርላንድስ እንዲሁም በአውሮፓ ኅብረት አገሮች መካከል የግብርና ንግድ ሥራን በቀላሉ ለመሥራትና የሥራ ፈጣሪዎችንም ለማገናኘት ምቹ ይሆናል ብለዋል፡፡

በኤምባሲው የግብርና አማካሪ የሆኑት ጆፕ ቫን ደን ብሩክ እንደተናገሩት፣ ሥራ ጀማሪ ወጣቶች በኢትዮጵያ የሚገጥማቸው ችግር ቀላል ባለመሆኑ በሁለቱ ወገኖች ትብብር የተጀመረው

ፕሮጀክት በተለይ በግብዓት አቅርቦት፣ በመስኖ ሥራ፣ በዘር እንዲሁም በግብርና ማቀነባበር ለሚሰማሩ ትኩረት የሚሰጥ ይሆናል፡፡ በቅመማ ቅመም፣ በዘር፣ በማር ማነብ ሥራና በአኩሪ አተር ዘርፎች የሚሰማሩም የመጀመርያው የመጀመርያውን ድጋፍ የሚያገኙት ይሆናሉ፡፡

በፕሮጀክቱ መሠረት በኢትዮጵያና

በኔዘርላንድስ መካከል የንግድ ልውውጥ እንደሚደረግ ሲጠበቅ፣ የንግድ ምክር ቤቱ ዋና ጸሐፊ አቶ ጌታቸው ረጋሳም ተገቢ ሆነው ለተገኙ የንግድ ሥራ ዕቅዶች ፈንድ እንደሚዘጋጅ አስታውቀዋል፡፡

የኔዘርላንስ መንግሥት ከአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የቆየ የትብብር

ግንኙነት እንዳለው አቶ ጌታቸው ሲጠቅሱ፣ ምክር ቤቱ በመርካቶ የዘረጋውን ፕሮጀክት በአነስተኛ ሥራዎች ላይ ለተሰማሩ ሴቶች የሥልጠናና የማማከር ድጋፍ ከመስጠት ባሻገር ንግድ ምክር ቤቱ ላቋቋመው ዓለም አቀፍ የንግድ ጉዳዮች የግልግል ፍርድ ቤትም መመሥረት ትልቅ ድጋፍ እንደሰጠ ለማወቅ ተችሏል፡፡

አዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ከኔዘርላንድስ ኤምባሲ ጋር የግብርና ንግድ ድጋፍ መስጠት ሊጀምር ነው

አምባሳደር ሃንስ ብላንክንበርግ አቶ አያሌው ዘገየ

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/መስፍ

ን ሰሎ

ሞን

Page 9: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 9 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

በዳዊት ታዬ

የምዕተ ዓመቱን የልማት ግቦች ተፈጻሚ ለማድረግ ኢትዮጵያን ጨምሮ እ.ኤ.አ በ2000 ቃል የገቡ አገሮች ብዛት 189 ነው:: ከእነዚህ አገሮች መካከል ደግሞ ለድኅረ 2015 የምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች ማዕቀፍ ዝግጅት፣ አገራዊ ምክክር እንዲያካሂዱ ከተመረጡ 50 አገሮች መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ናት::

ይህንኑ ተከትሎ በኢትዮጵያ የድኅረ 2015 የምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች አገር አቀፍ ምክክር በመላ አገሪቱ በአምስት ዙሮች እየተካሄደ ይገኛል:: ለዚሁ ግብ እስካሁን ከተካሄዱ የምክክር መድረኮች መካከል ትናንት በደሳለኝ ሆቴል የተካሄደው የብሔራዊ ምክክር አጀንዳ የግሉን ዘርፍ ማዕከል ያደረገ ነበር:: የምዕተ ዓመቱን ግቦች በመንተራስ የግሉ ዘርፍ ፍላጎትን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ሙሉ ሰለሞን፣ የግቦቹ ዝግጅት የመሠረታዊ ዓላማዎች ፍላጎትን መሠረት ባደረጉ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በማድረግ ያለውን ውስን ሀብት ወደተፈለገው አቅጣጫ በማሰባሰብ በተገቢው ሁኔታ መጠቀም ያስፈልጋል ብለዋል::

በ1992 ዓ.ም. በተካሄደው የምዕተ ዓመቱ ግቦች ጉባዔ ወቅት ከተቀረፁት ስምንቱ ግቦች በአምስቱ ኢትየጵያ የተሻለ ውጤት እንዳስመዘገበች መረጃዎች እንደሚያመላክቱ የተናገሩት ወ/ሮ ሙሉ፣ ያልተጠናቀቁትንና ተጨማሪ ግቦችን አካቶ ለመጓዝ የግል ዘርፉ ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል::

በዚህ መሠረት ባጠቃላይ ሰባት የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረኮች የሚዘጋጁ ሲሆን፣ አንደኛው የግሉ ዘርፍ ድምፅ የሚሰማበትና እ.ኤ.አ ከ2015 በኋላ ኢትዮጵያ ትኩረት ሰጥታ ልትንቀሳቀስባቸው በሚገቡ የልማት አቅጣጫዎች ላይ ግብዓት የሚሆኑ ሐሳቦችና አስተያየቶች የሚሰበሰቡበት ይኸው አንዱ መድረክ መሆኑን ወ/ሮ ሙሉ ገልጸዋል::

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ የተቀመጡትንና ትኩረት የተሰጣቸው የኢንዱስትሪ መስኮች ተገቢ መሆናቸውን የገለጹት ወ/ሮ ሙሉ፣ ሊተኮርባቸው ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮችም ጠቅሰዋል:: በተለይ ሰፋፊ የግል እርሻ ልማት፣ የእንስሳት ሀብት ልማትና ግብይት፣ አግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ቱሪዝምና የማዕድን ልማት መስኮች በመጭው የግብ ዝግጅት ትኩረት እንዲሰጣቸው ምክር ቤታቸው እንደሚሻ ጠቅሰዋል::

የንግዱ ማኅበረሰብ ተወዳዳሪ መሆን እንዲችል አቅምን የማሳደግ፣ የንግድ ልማት፣ የአገልግሎትና የጥራት ቁጥጥር ተቋማትን በማስፋፋትና ለመወዳደር ምቹ የሆነ የፖሊሲና የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖር በማድረግ የገበያ አድማስን ማስፋት ያስፈልጋልም ተብሏል::

የምዕተ ዓመቱ ግቦችን ለማሳካት የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕ፣ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የሚያመርቱ የትምህርት ተቋማትና የትምህርት ሥርዓት፣ የጎለበተ የሥራ ባህል፣ አምራች ዜጋ መፍጠር የሚያስችሉ ፖሊሲዎችና ድንጋጌዎች ለግሉ ዘርፍ ብሎም ለአገሪቱ ሶሺዮ-ኢኮኖሚክ ትራንስፎርሜሽን መሠረታዊ አጀንዳዎች መሆን እንደሚገባቸው የምክር ቤቱ እምነት መሆኑ ተገልጿል::

የድኅረ 2015 የምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች አጀንዳዎችና የግል ዘርፍ ሚናን በተመለከተ በተካሄደው በዚሁ ውይይት ላይ የተገኙት የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትር ዴኤታው ዶ/ር አብርሃም ተከስተ ከዚህ የምክክር መድረክ የሚገኙት ሐሳቦች ለመንግሥት ዕቅድ ተፈጻሚነት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው አመልክተዋል:: እንዲህ ካለው የምክክር መድረክ የሚገኙ ሐሳቦችን የአምስት ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ከተጠናቀቀ በኋላ አገሪቱ ለምታዘጋጀው ቀጣይ ዕቅድ በግብዓትነት እንደሚወሰዱ አስታውቀዋል::

ኢትዮጵያ በፖሊሲዎችና በልማት ዕቅዶች ዜጎችን በማሳተፍ የበሰለ አሠራር ሥርዓትና ልምድ እንዳላት የተናገሩት ዶ/ር አብርሃም፣ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን በምሳሌነት ጠቅሰዋል:: ይህ ዕቅድ ሰፊ ተሳትፎ የተደረገበትና

የግሉ ዘርፍ የመከረበት መሆኑንም አስታውሰዋል:: ከዚህ አንፃር የተጀመረው የድኅረ 2015 የምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች ማዕቀፍ አገራዊ ምክክር በተለይ በግሉ ዘርፍ የላቀ ተሳትፎ ተሳክቶ እንደሚፈጸም በመግለጽ፣ ለዚህም መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል::

በዕለቱ በኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት አማካሪዎች ተዘጋጅቶ በቀረበው ጥናት ላይ፣ የግሉ ዘርፍ በድኅረ 2015 የምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦችን አስመልክቶ በአገር አቀፍ ደረጃ በሚዘጋጀው ሰነድ ላይ መካተት ይገባቸዋል ያላቸውን የተለያዩ ሐሳቦች አስፍሯል::

በጥናቱ እንደተመለከተው፣ በኢትዮጵያ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ወዲህ፣ መንግሥት በኢኮኖሚው ውስጥ መሪነቱ እየጨመረ መሄዱን ጠቁመዋል:: በተጨማሪ አዳዲስ እየወጡ የሚገኙት መመርያዎችና ደንቦች አንዳንድ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንደፈለጉ እንዳይጓዙ ችግር ፈጥሯል ይላል::

ይኸው ጥናት የመንግሥት ዘርፉ በአንፃራዊነት ጠቃሚነቱ አይካድም ቢልም፣ በመሠረተ ልማትና በአምራችነት ዘርፍ ያለው ሚና እየጨመረ መምጣቱ በጥናቱ ቀርቦ በማክሮ ኢኮኖሚው የግሽበትና የምንዛሪ ምጣኔ ችግሮች የተነሳ በተፈጠረው አለመረጋጋት የንግዱ አካባቢን ሊጎዳው መቻሉም ተመልክቷል::

በቀጣይ ጊዜ ፈተና ይሆናሉ ተብለው ከተቀመጡ ነጥቦች መካከል የማክሮ ኢኮኖሚው አለመረጋጋት፣ የአገሪቱን ኢኮኖሚ በተመለከተ የሚወጡት አሃዛዊ መረጃዎችና የሚሰጡት ጠቀሜታ ውስን መሆኑ፣ ከታክስ ጋር በተያያዘ የሚነሱ አቤቱታዎች፣ የሚከለፈው መጠን ከፍተኛ መሆን በቀዳሚነት በጥናቱ ተቀምጠዋል:: ከዚህም ሌላ ከመሬት ፖሊሲው ጋር በተያያዘ መሬት ለማግኘት የሚወስደው ረጅም ጊዜ፣ የሊዝ ዋጋ ከፍተኛነት፣ በመንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶች መካከል ያለው የግንኙነትና የመረጃ ልውውጥ

ደካማነት እንደፈተና የሚታዩ ስለመሆናቸው ጥናቱ ያመለክታል::

በአገሪቱ የመሠረተ ልማት ጥራቱ በደካማ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጥናቱ አመልክቶ የሙስና አስከፊነት እየጨመረ መሄዱን፣ የገበያ አወቃቀር ምሉዕነት የጎደለው መሆኑንና የመጫወቻ ሜዳው ሥርዓትን ያልጠበቀ መሆኑን የተመለከተው ጥናቱ፣ የመንግሥትና የግሉ ዘርፍ ትብብርም በሚፈለገው ደረጃ አለመሄዱን ከችግሮች አንዱ አድርጐታል:: መንግሥት በግሉ ዘርፍ ሊሠሩ በሚችሉ ዘርፎች ውስጥ እየገባ መምጣቱንም ጠቁሟል:: በሌላ በኩል የአገሪቱ የሠራተኛ ሕግ የንግዱን ዘርፍ ውጤታማና ጠንካራ እንዳይሆን መገደቡን ጠቅሶ፣ የሠራተኛ ጉዳይን የሚመለከቱ ፍርድ ቤቶች የሚሰጡት ውሳኔ፣ ቀጣሪዎችን ዋጋ የሚያስከፍልና ውሳኔውን በማስከበር ሒደት ጊዜ እንዲባክን እያደረገ ነው ተብሏል::

በቂ የድጋፍ ሰጪ አገልግሎት ባለመኖሩ የተነሳ ቢዝነስ ነክ የሆኑ መረጃዎች በተለይ የገበያ ደረጃ፣ ዋጋ፣ የምርት ተደራሽነት ዝቅተኛ መሆኑን ጥናቱ ያመለክታል:: በተጨማሪም በንግድ ሕጉ የተቀመጠው መቀጫ ከፍተኛነትን በተመለከተ፣ ጥናቱ የንግድ አፈጻጸምና የደንበኞች ጥበቃ ሕግን ለአብነት አስቀምጧል::

በአገራዊ ምክክሩ በምዕተ ዓመቱ ግቦች መካተት ይገባቸዋል በማለት በርካታ ጉዳዮችን ተጠቁመዋል:: በዋነኝነት፣ የግሉ ዘርፍ የልማት ስትራቴጂ ማዘጋጀት፣ የአገሪቱን ኢኮኖሚ የሚያመለክቱ አሃዛዊ መረጃዎች ውጤታማነታቸውን እንዲጨምሩ ማድረግ፣ መንግሥት የሚያወጣቸው ፖሊሲዎች ተፈጻሚነታቸው እንዲጨምር የሚሻሻሉበትን ሥርዓት እውን ማድረግ፣ ለቴክኖሎጂ ሽግግር ወሳኝ የሆኑ ስልቶችን ተግባራዊ ማድረግ የሚሉት ይገኙበታል::

መንግሥታዊ ተቋማትን በዘመናዊ መንገድ እንዲተከሉ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን መሥራት እንደሚገባ በጥናቱ የተጠቆመ ሲሆን፣ ሕገ

መንግሥቱን መሠረት በማድረግ የፍትሕ አካላት ሥራቸውን በነፃነት የሚከናወኑበትን ሥርዓት እንዲኖርም ተጠቁሟል::

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግል ባንኮች 27 ከመቶ ቦንድ እንዲገዙ የሚያስገድደው መመርያ በድጋሚ ሊጤን እንደሚገባ ተጠቅሶ፣ በአገሪቱ የአክሲዮን ገበያ ለማቋቋም የሕግ ማዕቀፍ በመፍጠር፣ ያን የሚመራ ተቋም እውን የሚሆንበትን አሠራር መከተል ይገባል ተብሏል::

በኢትዮጵያ የንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት አማካይነት በተዘጋጀው የጥናት ወረቀት ውስጥ በርካታ ሊሻሻሉ የሚገባቸው ሐሳቦች የቀረቡ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲን ብቃት ከማጠናከር ጀምሮ የግሉ ዘርፍ ደረጃዎችን የሚላኩ ላብራቶሪዎችን በዘርፍ ውስጥ እንዲካተቱ ጥናቱ ጠይቋል::

የአገሪቱ የንግድ ውድድር ሁሉም በእኩልነት የሚወዳደሩበት መሆን እንደሚገባው ጥናቱ ጠቁሞ፣ የውድድር ሕግን ተፈጻሚነት የሚያሻሽሉ ሕጎች ተግባር ላይ ቢውሉ ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነ አመልክቷል:: ከዚህም ሌላ፣ የጥናትና የምርምር ተቋማት በአገሪቱ ውስጥ እየተካሄደ ካለው የኢንዱስትሪ ልማት ጋር ጥምረት ፈጥረው የሚሠሩበት ሁኔታ ቢመቻች ጠቃሚ መሆኑን ጠቁሞ፣ በተለይ የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚከተሉት ድርጅቶች ልዩ ማበረታቻ እንዲያገኙ ቢደረግ ተመራጭነቱ ከፍተኛ ነው ብሏል::

የኢትዮጵያ አምራቾች የላኪነት ሚናቸው እየጨመረ እንዲሄድ ዘርፉን የሚደግፍ መንግሥታዊ የሆነ የኤክስፓርት ፕሮሞሽን አገልግሎት የተባለ ተቋም እንዲመሠረት ተጠይቋል:: ከግል ዘርፉ የቀረቡ ሐሳቦችና በመንግሥት በኩል የተሰጡ አስተያየቶች ላይ የውይይቱ ተካፋዮች ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ መጨመር ይገባቸዋል ያሏቸውንም ሐሳቦች አቅርበዋል::

የምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦችና የግሉ ዘርፍ

ወ/ሮ ሙሉ ሰለሞን እና ዶ/ር አብርሃም ተከስተ

Page 10: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 10|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

Action For Development (AFD)Vacancy Announcement

Action For Development (AFD), an Ethiopian Residents Charity, would like to invite applicants for the following position; Position – Water Resources and Rural Infrastructural Development Officer IQualification − BSc Degree/Diploma in Civil, Hydraulics, Irrigation or Water Resources

Engineering or Construction Management; Experience− At least 2 years for BSc Degree or 4 years for diploma of relevant experience

in water resources development and related works in all aspects of study, design and implementation. NGO experience is preferable.

Requirements− Computer skill particularly in Microsoft Word, Power Point, etc;− Skill and enriched experience in Auto CAD and Water CAD/EPANET and

other common Engineering software; − Good interpersonal and communication skills. Job Summary− Responsible for proper planning, implementation, quality and effective delivery

of physical development infrastructures in relation to Water supply, sanitation

and hygiene (WaSH) project including the software activities in relation to the services developed at ABECs (ABEC) and the surrounding community;

− Actively participate at and ensure coordination and facilitation of technical and behavioral related trainings and awareness raising sessions related to school WaSH interventions;

− Survey, study and design various water and rural infrastructure development projects (WaSH, Irrigation Schemes, Schools, Offices & so on);

− Prepares drawings, work and material specifications, work plans and procurement plans and follow up the implementation of different construction activities to ensure compliance with designs, standards, and existing norms & provide the required technical assistance for the construction crew;

− Follow up and ensures full participation of communities and counter parts in project activities;

− Lialses with line departments, NGOs and other concerned stakeholders for the smooth implementation of projects;

Duty Station – South Omo Zone, Hamer Woreda, TurmiTerms of Employment – Six months contract (renewable)Salary: As per the organization’s Scale Application: Letter of application, CV, relevant credentials, & three letters of recommendation should be submitted to: Head Office, Addis Ababa; Application Deadline: 10 days from the date of this notice; Only short listed candidates will be contacted & documents will not be returned.

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያቤቴል ቲቺንግ ጠቅላላ ሆስፒታል ከዚህ በታች በተጠቀሰው ክፍት የሥራ መደብ ብቁ ባለሙያዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል::

ተ.ቁየሥራ መደቡ

መጠሪያየትምህርት ደረጃ ብዛት የሥራ ቦታ ደመወዝ

የቅጥር ሁኔታ

የሥራ ልምድ ጾታ

1 ፖርተር 8ኛ ክፍል ያጠናቀቀ 4 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 0 ዓመት የሥራ ልምድ ወ

2 ካሸር አካውንቲንግ ዲፕሎማ ያለው/ያላት 2 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 1 ዓመት የሥራ ልምድ ያለውና በpos-Land ማሽን ላይ መስራት የሚችል/የምትችል

ሴ/ወ

3 ሾፌር 10ኛ ክፍል 2 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 4ኛ መንጃ ፍቃድ ያለውና ቢያንስ 2 ዓመት የስራ ልምድ ያለው ወ

4 ሾፌር 10ኛ ክፍል 3 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 3ኛ መንጃ ፍቃድ ያለውና ቢያንስ 2 ዓመት የስራ ልምድ ያለው ወ

5 የካፍቴሪያ ኃላፊ በድሮ 12ኛ ክፍል የጨረሰ በአሁኑ 10ኛ ክፍል

1 አዲስ አባባ በስምምነት በቋሚነት 2 ዓመት የሠራ/ች

6 ለካፍቴሪያ

አስተናጋጅ

10ኛ ክፍል ያጠናቀቀ/ች 3 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት ቢያንስ 1ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት ሴ/ወ

7 ምግብ ዝግጅት ዲኘሎማ 3 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት በምግብ ዝግጅት ቢያንስ 1 ዓመት በሙያው የሰራ/ች ሴ/ወ

8 በምግብ ዝግጅት ክፍል ውስጥእንጀራ

መጋገር

ማንበብና መፃፍ የምትችል 1 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት በድርጅት ውስጥ ቢያንስ 1 ዓመት በሙያው የሰራ/ች

9 ፅዳት 4ተኛ ክፍል የጨረሰ 3 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 0 ዓመት የሠራች ሴ

ቤቴል ቲቺንግ ጠቅላላ ሆስፒታል ከዚህ በታች በተጠቀሰው ክፍት የሥራ መደብ ብቁ ባለሙያዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል::

ተ.ቁ የሥራ መደቡ መጠሪያ የትምህርት ደረጃ ብዛት የሥራ ቦታ ደመወዝ የቅጥር ሁኔታ የሥራ ልምድ ጾታ

1 ፖርተር 8ኛ ክፍል ያጠናቀቀ 4 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 0 ዓመት የሥራ ልምድ ወ

2 ካሸር አካውንቲንግ ዲፕሎማ ያለው/ያላት 2 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 1 ዓመት የሥራ ልምድ ያለውና በpos-Land ማሽን ላይ መስራት የሚችል/የምትችል

ሴ/ወ

3 ሾፌር 10ኛ ክፍል 2 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 4ኛ መንጃ ፍቃድ ያለውና ቢያንስ 2 ዓመት የስራ ልምድ ያለው

4 ሾፌር 10ኛ ክፍል 3 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 3ኛ መንጃ ፍቃድ ያለውና ቢያንስ 2 ዓመት የስራ ልምድ ያለው

5 የካፍቴሪያ ኃላፊ በድሮ 12ኛ ክፍል የጨረሰ በአሁኑ 10ኛ ክፍል

1 አዲስ አባባ በስምምነት በቋሚነት 2 ዓመት የሠራ/ች

6 ለካፍቴሪያ አስተናጋጅ 10ኛ ክፍል ያጠናቀቀ/ች 3 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት ቢያንስ 1ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት ሴ/ወ

7 ምግብ ዝግጅት ዲኘሎማ 3 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት በምግብ ዝግጅት ቢያንስ 1 ዓመት በሙያው የሰራ/ች

ሴ/ወ

8 በምግብ ዝግጅት ክፍል ውስጥእንጀራ መጋገር

ማንበብና መፃፍ የምትችል 1 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት በድርጅት ውስጥ ቢያንስ 1 ዓመት በሙያው የሰራ/ች

9 ፅዳት 4ተኛ ክፍል የጨረሰ 3 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት 0 ዓመት የሠራች ሴ

አድራሻ፣ ቤቴል ቲቺንግ ጠቅላላ ሆስፒታልቁጥር 1 ቢሮ ቁጥር 114

ስልክ 251-011-349 54 75/76/77 ፋክስ፡ 251-011-349 58 39ፖ.ሣ.ቁ. 9011፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ

Page 11: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 11 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ማስታወቂያ

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ማህበር ከዚህ በታች ለተገለጹት ክፍት የሥራ መደቦች ባለሙያዎችንና አሰልጣኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

በዚህም መሰረት አመልካቾች ያላችሁን ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ መረጃዎች በመያዝ ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንጻ 2ኛ ፎቅ ቁጥር 205 በግንባር ቀርባችሁ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናቶች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን የስፖርት ማህበሩ ያሳውቃል፡፡

1. የቅጥር ሁኔታ - ለአንድ አመት ኮንትራት ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ የሚራዘም ይሆናል፡፡2. ጾታ ___ አይለይም3. ዕድሜ 18 አመትና ከዚያ በላይ የሆነ/የሆነች4. ደመወዝ ___ በስምምነት

ተ.ቁየስራ መደቡ መጠሪያ

ብዛት ተፈላጊ የት/ደረጃና የሥራ ልምድ

1.

የእግር ኳስ ስፖርት ባለሙያ 1

በስፖርት ሳይንስ ወይም በሰውነት ማጐልመሻ ትምህርት ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት

በእግር ኳስ ስፖርት በሀገር ውስጥ የአሰልጣኝነት ም/ወረቀት ያለው/ያላት

በሙያው ቢያንስ ሁለት አመትና ከዚያ በላይ የሠራ/የሠራች

በFIFA ወይም በCAF የተወሰዱ የአሰልጣኝነት ስልጠናዎች ካለው/ካላት ተመራጭ ይሆናል

የእግር ኳስ ቡድኖችን በማስተባበር ድጋፍ መስጠት የሚያስችል ልምድ ያለው ያላት

ለስራ መደቡ የሚሰጠውን የተግባርና የፅሁፍ ፈተና መሳተፍ የሚችል/የምትችል

የእግር ኳስ ህጐችን በሚገባ የሚያውቅ/የምታውቅ ቢሆን ይመረጣል

በሙያው የተለያዩ ችግር ፈቺ ማንዋሎች፣ መመሪያዎች ደንቦችና ጥናቶችን የማዘጋጀት ልምድ እና ብቃት ያለው/ያላት

በስፖርት የተለያዩ መድረኮች ላይ አስተዋፅኦ ማበርከቱ/ ማበርከቷ በም/ወረቀት የሚረጋገጥ

የኮምፒውተር መሰረታዊ ዕውቀት ያለውና የም/ወረቀት ማቅረብ የሚችል/የምትችል

ተ.ቁየስራ መደቡ መጠሪያ

ብዛት ተፈላጊ የት/ደረጃና የሥራ ልምድ

2.

የአትሌቲክስ ስፖርት ባለሙያ 1

በስፖርት ሳይንስ ወይም በሰውነት በጐልመሻ ትምህርት ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት

በአትሌቲክስ ስፖርት በሀገር ውስጥ የአሰልጣኝነት ም/ወረቀት ያለው/ያላት

በሙያው ቢያንስ ሁለት አመትና ከዚያ በላይ የሠራ/የሠራች

በIAAF ወይም በCAA የተወሰዱ ስልጠናዎች ካለው ተመራጭ ይሆናል

የአትሌቲክስ ቡድንን በማስተባበር ድጋፍ መስጠት የሚችል ልምድ ያለው/ያላት

የስራ መደቡ ላይ የሚሰጠውን የተግባርና የጽሁፍ ፈተና መሳተፍ የሚችል/የምትችል

የአትሌቲክስ ስፖርት የዳኝነት ህጐችን በሚገባ የሚያውቅ/የምታውቅ ቢሆን ይመረጣል

በሙያው የተለያዩ ችግር ፈቺ ማንዋሎች፣ መመሪዎች፣ ደንቦችንና ጥናቶችን የማዘጋጀት ልምድና ብቃት ያለው

በስፖርት የተለያዩ መድረኮች አስተዋፆኦ ማበርከቱ/ቷ በም/ወረቀት የሚረጋገጥ

የኮምፒውተር መሰረታዊ ዕውቀት ያለው/ያላትና የም/ወረቀት ማቅረብ የሚችል/የምትችል

3.

የአትሌቲክስ ስፖርት ረዳት አሰልጣኝ

2

በስፖርት ሳይንስ ወይም በሰውነት ማጐልመሻ ትምህርት ቢያንስ ዲፕሎማና ከዚያ በላይ የት/ደረጃ ያለው/ያላት

በአትሌቲክስ ስፖርት አሰልጣኝነት ሙያ ቢያንስ 2 አመትና ከዚያ በላይ ያገለገለ/ያገለገለች

በአትሌቲክስ ስፖርት የሀገር ውስጥ ሁለተኛ ደረጃ አሰልጣኝነት ስልጠና የወሰደ/የወሰደች

በIAAF የተሰጡ ስልጠናዎች አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የወሰደ/የወሰደች ተመራጭነት ይኖረዋል/ይኖራታል

ከዚህ ቀደም በሌሎች ክለቦች ላይ አገልግሎት የሰጠና ስለብቃት ማረጋገጫ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል/የምትችል

የሚሰጠውን የጽሁፍና የተግባር ፈተና ለመውሰድ ሙሉ ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች

በተለያዩ የአትሌቲክስ ተግባር (ኢንቨንት) ላይ ተመድቦ መስራት የሚችል/የምትችል

የኮምፒውተር መሰረታዊ ዕውቀት ያለው/ያላትና የም/ወረቀት ማቅረብ የሚችል/የምትችል

የአትሌቲክስ ስፖርት ስልጠና በሚሰጥባቸው ክለቦች ውስጥ አሰልጥኖ ውጤታማ መሆኑን/መሆኗን የሚገልፅ የድጋፍ ደብዳቤ ከሀገር አቀፍና ከክልል ፌዴሬሽን ማቅረብ የሚችል/የምትችል::

ማስታወሻ፡- አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርት ማስረጃችሁን፣ የስራ ልምዳችሁንና አጋዥ መረጃዎችን ኦሪጅናልና አንድ ፎቶ ኮፒ በመያዝ በግንባር ቀረባችሁ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ስልክ ቁጥር 011-122-88-24

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ማህበር

የሚለው ግምት አይሎ ነበር:: ነገር ግን ከበርካቶች ግምት ውጪ ዶ/ር ቴድሮስ የውጭ

ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል:: ዶ/ር ቴድሮስ በጤናው መስክ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወን በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አድናቆት የተቸራቸው ናቸው::

የኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ ከሚጠይቀው የውጭ የገንዘብ ድጋፍና ዕርዳታ አንፃርም፣ ዶ/ር ቴድሮስ በነበራቸው ተሰሚነት ምክንያት በሚኒስትርነት ይመሩት የነበረው የአገሪቱ የጤና ዘርፍ ተጠቃሚ ሆኖ ቆይቷል::

ዶ/ር ቴድሮስ ያገኙት ዓለም አቀፍ ተሰሚነት በጤናው ዘርፍ ላይ ብቻ ከመሆኑና እንዲሁም ኢትዮጵያ ካለችበት የአፍሪካ ቀንድ የሰላምና ፀጥታ ችግር አንፃር፣ በውጭ ጉዳይ

ሚኒስቴር ከባድ ሥራ ይጠብቃቸዋል የሚሉ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ነው::

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ከተሾሙ ገና ሁለት ሳምንታትን ብቻ ያስቆጠሩት ዶ/ር ቴድሮስ፣ በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ከሚገኙ አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ጋር የሚያደርጉት ትውውቅ የመጀመሪያው ይፋዊ የዲፕሎማሲ ተግባራቸው ይሆናል::

በዛሬው ዕለት ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር በመሆን ለተመረጡት ደቡብ አፍሪካዊቷ ዶ/ር ን ኮሳዛና ድላሚኒ ዙማ የእራት ግብዣ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል::

የውጭ ጉዳይ... ከገጽ 1 የዞረ

ሪፖርት እንደሚገልጸው፣ ለዘጠኝ የአገር ውስጥ ድርጅቶች የሽያጭ መመዝገቢያ መሣርያዎችን ከውጭ በማስገባት ለተጠቃሚዎች እንዲያቀርቡ በተሰጣቸው ዕውቅናና ፈቃድ መሠረት፣ በአጠቃላይ በአገር አቀፍ ደረጃ አቅራቢዎቹ መሣርያውን የመጠቀም ግዴታ ላለባቸው 50,883 ግብር ከፋዮች 60,159 መሣርያዎችን ሸጠዋል::

ይሁን እንጂ ወደ ሥራ ከገቡት እነዚህ መሣርያዎች ውስጥ 50 በመቶ የሚሆኑት የሽያጭ መረጃዎችን ወደ ባለሥልጣኑ የመረጃ ቋት እየላኩ እንዳልሆነ፣ የባለሥልጣኑ የሽያጭ መመዝገቢያ መሣሪያዎች ጉዳይ አስተባባሪ አቶ አንተነህ ታምራት ለሪፖርተር ገልጸዋል::

እያንዳንዱ የሽያጭ መመዝገቢያ መሣርያ እንደ ሞባይል ስልክ አገልግሎት በሚገጠምለት ሲም ካርድ አማካይነት በየጊዜው የሚካሄዱ ግብይቶችን ለባለሥልጣኑ የታክስ መረጃ ቋት የሚልክበት ሥርዓት ቢዘረጋም፣ መረጃው የሚተላለፍበት የኢትዮ ቴሌኮም የኔትወርክ አገልግሎት ግን ሥርዓቱን እየደገፈ አይደለም ብለዋል::

እያንዳንዱ የሽያጭ መመዝገቢያ መሣርያ የቴሌን ኔትወርክ በመጠቀም ለሚልከው መረጃ ባለሥልጣኑ አንድ ሲም ካርድ ለሚጠቀመው የአየር ሰዓት 350 ብር ለቴሌ እንደሚከፍል የሚናገሩት አቶ አንተነህ ችግሩን አስመልክቶ ከኢትዮ ቴሌኮም ኃላፊዎች ጋር የተደረገው ተደጋጋሚ ውይይትም መፍትሔ አላመጣም ብለዋል::

መሣሪያዎቹ የሽያጭ መረጃቸውን በዚህ ኔትወርክ መላክ ባለመቻላቸው፣ ግብር ከፋዮች መሣርያዎቻቸው የመዘገቡትን ሽያጭ በወረቀት ለባለሥልጣኑ እንዲያቀርቡ መደረጉን ገልጸዋል::

ይህ የመፍትሔ ዕርምጃ የወረቀት ሥራዎችን በግብር

ከፋዩና በባለሥልጣኑ ላይ ከመጨመሩም በላይ፣ በሽያጭ መረጃው ላይ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ገልጸዋል::

ከኢትዮ ቴሌኮም በኩል እየተሰጠ ያለው ምላሽ መሣርያዎቹ የሚጠቀሙበት ኔትወርክ አቅም ማነስ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት 40 በመቶ የሚሆነው አቅም መረጃውን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል የሚል ነው:: ነገር ግን ቴሌ እንደሚለው መረጃው እየመጣ አይደለም ሲሉ አቶ አንተነህ ተናግረዋል::

‹‹የኔትወርክ መቆራረጥ ቢሆን እንኳን መሣርያዎቹ ኔትወርኩን ባገኙ ጊዜ ሳያስተላልፉ ያጠራቀሙትን መረጃ በአንድ ጊዜ ሊልኩ ይችሉ ነበር:: ነገር ግን ይህ እየሆነ አይደለም በመሆኑም ኔትወርኩ እየሠራ አይደለም፤›› ሲሉ አክለዋል::

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ደግሞ ባለሥልጣኑ የሚጠቀመው የኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎቱን እየሰጠ እንዳልሆነ ለሪፖርተር ገልጸዋል:: ኔትወርኩ ኖኪያ በተባለው ኩባንያ ከዚህ ቀደም የተሠራ ሲሆን፣ ኢትዮ ቴሌኮም ለኩባንያው ሙሉ ክፍያ ባለመፈጸሙ ኔትወርኩን በመጠገንና በማስፋፋት ወደ ሥራ መመለስ አልተቻለም:: በሌሎች ኩባንያዎች ለማስጠገን ደግሞ የኖኪያን ቴክኖሎጂን ማወቅ ከመጠየቁም ባሻገር የኩባንያውን ፈቃድ ማግኘትን ይጠይቃል ብለዋል::

ጉዳዩን አስመልክቶ ለኢትዮ ቴሌኮም የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አብዱራህማን አህመድ በተደጋጋሚ ያደረግነው የስልክ ጥሪ ምላሽ አላገኘም:: በሞባይል ስልካቸው መልዕክት መቀበያ ላይ ጉዳዩን በመግለጽ እንዲደውሉልን መልዕክት በመተው ያደረግነው ጥረትም አልተሳካም::

ገቢዎች ባለሥልጣን... ከገጽ 1 የዞረ

ዶክተር መጥተው የባለቤቷን ስልክ ሲጠይቋቸው፣ “ምነው ልጄ ምን ሆነች?” ሲሏቸው፣ “ደም ስላነሳት ደም እንዲሰጥ ነው” እንዳሏቸው ተናግረዋል::

የቤተልሔም ባለቤትና ጓደኞች ደም ቢሰጡም እየደከመች ስለመጣችባቸው ያዋለዷት ዶክተር ሪፈር ጽፈው በመስጠት ኦክስጂን የተገጠመለት አምቡላንስ እንዲያመጡ ይነግሯቸዋል:: ደክማለች በተባለችው ልጃቸው የተጨናነቁት ቤተሰቦች፣ ሩጫቸውን ወደ ተክለሃይማኖት ሆስፒታል እንዳደረጉ ይናገራሉ:: የተጻፈውን ሪፈር ወረቀት የተመለከቱት የተክለሃይማኖት ሆስፒታል ሐኪም፣ “ብዙ ደም ስለፈሰሳት አንሠራም፤ ኃላፊነት አንወስድም፤” ሲሏቸው እግራቸው ሥር ቢወድቁም ሌላ ምላሽ ሊሰጧቸው እንዳልቻሉ ገልጸዋል::

ግራ የተጋቡት ቤተሰቦች ጉዟቸውን ሜክሲኮ ገነት ሆቴል አካባቢ ወደሚገኘው ላንድማርክ ሆስፒታል በማድረጋቸው፣ የታዘዙትን ኦክስጂን የጫነ አምቡላንስ ማግኘታቸውን ተናግረዋል:: የሆስፒታሉ ሠራተኞች፣ “እናንተ እዚህ ጠብቁን፤ እኛ ይዘናት እንመጣለን፤” ብለው ቤተልሔም ወደተኛችበት ሮያል የጽንስና የማኅፀን ሕክምና ከፍተኛ ክሊኒክ በማምራት ይዘዋት መምጣታቸውን እናቷ ወይዘሮ በለጡ ተናግረዋል:: የቤተሰቦቿ መሯሯጥና እሷን ለማትረፍ ያደረጉት ጥረት ውጤት ሳያገኝ ቤተልሔም ላንድማርክ ስትደርስ ማረፏን እናቷና ባለቤቷ አስረድተዋል::

ይኼ ሁሉ የሆነው ኅዳር 28 ቀን 2005 ዓ.ም. ሙሉቀን እስከ ምሽት ድረስ በመሆኑ፣ የቤተልሔም አስከሬን ላንድማርክ ሆስፒታል እንዲያድር ይደረግና ቤተሰቦቿ በቀዶ ሕክምና የተወለደችውን ሕፃን ታቅፈው ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ::

“ማንኛውም እናት በወሊድ ምክንያት መሞት የለባትም” የሚለው መሪ ቃል ባልሠራበት ሁኔታ ደም ፈሷት ሕይወቷን መታደግ ሳይቻል በመቅረቱ ቤተልሔም ሕይወቷ ማለፉንም አስረድተዋል:: ቤተሰቦቿና ወዳጅ ዘመዶቿ በተገኙበት የቀብር ሥርዓቷ ገርጂ በሚገኘው ደብረገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ኅዳር 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት መፈጸሙን ቤተሰቦቿ አረጋግጠዋል::

የቀብር ሥርዓቷን ፈጽመው በሐዘን እየተብሰለሰሉ የዋሉትና ያደሩት የቤተልሔም ቤተሰቦች፣ በማግሥቱ ኅዳር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. የተነገራቸውን ማመን አቅቷቸው ወደ ቀብር ቦታዋ ተሯሩጠው ይሄዳሉ::

ቤተሰቦቿ የቀብር ቦታው ሲደርሱ የቤተልሔም አስከሬን ከተቀበረበት ጉድጓድ ወጥቶ ዳር ላይ በፊቱ ተደፍቶ ማየታቸውን ይገልጻሉ:: አስከሬን ጉድጓድ ውስጥ ከገባ በኋላ በባዞላ ድንጋይ ጉድጓዱ ተደፍኖ በላዩ ላይ በሲሚንቶ ይለሰናል:: ከዚያም በላይ አፈር ይለብሳል:: ይኼንን ሁሉ አልፎ እንዴት ሊፈጸም እንደቻለ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ሊቀ ማዕምራን ጽጌ ከበረ ምላሽ እንዲሰጡ በሪፖርተር ተጠይቀው ነበር::

አስተዳዳሪው እንደነገሩን፣ ሟች የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ በመሆኗ ሥርዓተ ፍትኃት ተፈጽሞላት ኅዳር 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት የቀብር ሥርዓቷ ተከናውኗል:: በዚያኑ ቀን ለእሑድ አጥቢያ እሳቸው ቅዳሴ ላይ እያሉ የቤተ ክርስቲያኑ ጥበቃዎች አስከሬን ከጉድጓድ ወጥቶ መገኘቱን ነግረዋቸዋል::

ጥበቃዎቹ እንደነገሯቸው አስከሬን ከተቀበረበት ወጥቶ በመገኘቱ ለፖሊስ ተደውሎለት መጥቷል:: የሟች ቤተሰቦችም መጥተዋል:: ውጭ ላይ የተገኘው አስከሬን የተገነዘበት ጨርቅም የለም:: አስከሬኑ ልብስ ባለመልበሱ ምክንያት ነጠላ ተሸፍኖ አባዲና እስኪመጣ ቢጠበቅም ሊመጣ ባለመቻሉ፣ ፖሊስና የሟች ቤተሰቦች ተመካክረውና

ተስማምተው ለሁለተኛ ጊዜ ኅዳር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ አምስት ሰዓት አካባቢ በድጋሚ ቀብሩ መፈጸሙን አስረድተዋል::

አስተዳዳሪው ያዩትን እንደተናገሩት፣ አስከሬኑ የወጣው ባንድ በኩል አንድ ባዞላ ድንጋይ ተፈንቅሎና በጠባብ ቀዳዳ ውስጥ ሲሆን፣ ቀብር የተፈጸመበት ሳጥንም ጉድጓዱ ውስጥ መሆኑንና አስከሬኑ በማበጡ ምክንያት እንዴት በዚያ ቀዳዳ ውስጥ እንደወጣ ተዓምር እንደሆነባቸው ነው::

አስተዳዳሪው እንደገለጹት ሁሉ የሟች ቤተሰቦች ያዩትን ተናግረዋል:: በሲሚንቶ የተደፈነ መቃብርን ደም ፈሷት የሞተች፣ ከ12 ሰዓታት በላይ ታፍና የቆየችና አቅም የሌላት ወላድ፣ ቀጭን ሰው በማያስወጣ ቀዳዳ እንዴት እንደወጣች፣ አፈሩ ሳይነሳና ከአንድ ባዞላ በስተቀር ሌላው ሳይነካ አስከሬን ወጥቶ በደረቱ ተደፍቶ መገኘቱ ግራ እንዳጋባቸው ተናግረዋል::

የሟች ቤተልሔም አስከሬን ጉዳይ በሁለት ጊዜ ቀብር ሳያበቃ ከተቀበረ ከሰዓታት በኋላ “ጩኸት ይሰማል፤ ሳጥን እየተንኳኳ ነው፤” በማለት ፖሊሶች፣ የወረዳ አስተዳዳሪዎችና ሕዝቡ አካባቢውን አጥለቅልቆት እንደገና መጠራታቸውን ቤተሰቦቿ ገልጸዋል:: እነሱ ሲደርሱ “ሆን ብለው ከነነፍሷ ቀብረዋት ነው፤ አምልኮ ቢኖር ነው፤ ስትጮህ ሰምተናታል፤ ውኃ ስጡኝ ስትል ነበር፣ ወዘተ” ከሚል ሹክሹክታና ትርምስ በስተቀር የቀብር ቦታው እንዳልተከፈተ መመልከታቸውን ቤተሰቦቿ ተናግረዋል::

ፖሊሶች የሟች ቤተሰቦችን “እኛም ምንም የሰማነውና ያየነው ነገር የለም፤ ፈቃደኛ ከሆናችሁ ይቆፈርና ይውጣ፤” የሚል ጥያቄ ሲያቀርቡላቸው፣ “የተሰበሰበው ሰው የተለያየ ነገር ሲል እየሰማን እንዴት አይሆንም እንላለን? ይቆፈርና ይውጣ፤” በማለት መፍቀዳቸውን ተናግረዋል::

አስከሬኑ በፖሊስ ተቆፍሮ እንዲወጣ ከተደረገ በኋላ ሳጥኑ ሲከፈትና አባዲና ሲመረምረው መሞቷ መረጋገጡን፣ ነገር ግን ሰውነቷ ፎርማሊን የተወጋ ቢሆንም፣ መተጣጠፍና መዘረጋጋት እንደሚችል የገለጹት ቤተሰቦቿ፣ ሕይወቷ ለማለፉ የመጨረሻ ማረጋገጫ ለማግኘት አስከሬኑ ዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ገብቶ እንዲመረመር ከተደረገ በኋላ፣ ለሦስተኛ ጊዜ ታኅሣሥ 1 ቀን 2005 ዓ.ም. ለመጨረሻ ጊዜ ቀብሯ መፈጸሙን አስታውቀዋል::

ልጃቸው በሕክምና ጉድለት ደሟ ፈሶ መሞቷ አንሶ አስከሬኗ ሲንገላታ መክረሙ የበለጠ መሪር ሐዘን እንደሆነባቸው የገለጹት እናቷ፣ አንድ ልጃቸው መሆኗንና እሳቸውም ሆኑ ልጃቸው ከማንም ጋር ፀብም ሆነ ቅያሜ የሌላቸው በመሆኑ የልጃቸውን አስከሬን ከጉድጓድ ያወጣውን ማወቅ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል:: መንግሥት “ሰምተናል፣ አይተናል፤” በማለት ሕዝቡንና ሐዘንተኞችን ሲያሸብሩ የነበሩትን በደንብ እንዲመረምርና ያለውን እውነት እንዲገልጽላቸውም ጠይቀዋል::

የባለቤታቸውን የአስከሬን ምርመራ ውጤትና በቁጥጥር ሥር የዋሉትን ተጠርጣሪ ሰዎች የምርመራ ውጤት አንድ ላይ ለቤተሰብና ለሕዝቡ ፖሊስ ይፋ እንዲያደርግ አቶ ፍሰሐ እሸቴ ጠይቀዋል::

ፖሊስ ስለደረሰበትና ስለተደረገው ነገር ሁሉ ማብራርያ እንዲሰጥ በሪፖርተር ጥያቄ ቀርቦለት፣ የአስከሬኑ ምርመራ ውጤት ገና እንዳልደረሰ ገልጾ፣ ሕዝብንና ቤተሰብን በተደጋጋሚ ሲያሸብሩ የነበሩትን በቁጥጥር ሥር ማዋሉንና በምርመራ ላይ መሆኑን አስታውቋል:: በምርመራ ላይ በመሆኑም ተጨማሪ ማብራርያ መስጠት እንደማይችል ገልጿል::

በሁለት ቀናት ልዩነት... ከገጽ 1 የዞረ

Page 12: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 12|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

Page 13: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 13 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ማስታወቂያ

Page 14: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 14|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

ማስታ

ወቂያ

(ጥንቅር- ብሩክ ቸርነት)

ጨረታ እና ንብረት (ጥንቅር- ዳዊት ወርቁ)

ግዥጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የኦሮሚያ

መንገዶች ባለሥልጣን:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የቀላል ተሽከርካሪዎች ጎማ:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ታህሣሥ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011-371-80-87/011-371-80-68 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የተለያዩ የእንሰሳት ላቦራቶሪ መገልገያ እቃዎችና ኬሚካሎች እና ወዘተ … ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0344 40 36 63/0344 40 43 46 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የኢትዮጰያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የላቦራቶሪ ግብዓቶች:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0116 46 05 45/0116 46 05 41 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 02 ጤና ጣቢያ:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የተለያዩ የህክምና መሣሪያዎችና የላቦራቶሪ ሬኤጀንቶች፣ አላቂ የህክምና ዕቃዎች የበረት ካዝና፣ የጽዳት ዕቃዎች ወዘተ … ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 663 63 63/0913 57 45 86 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የቃሊቲ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች ወዘተ … ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 439 55 67/04 47 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሥት የቤንች ማጂ ዞን ፋ/ኢ/ል/መምሪያ:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- ልዩ ልዩ መጻሕፍት:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0922 69 54 55/ 047 335 05 76 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ማኅበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የጽሕፈት መሣሪያዎችና ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 371 02 91 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የተለያዩ መጻሕፈትና የላቦራቶሪ ዕቃዎች:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0255 53 00 16 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- ቋሚ ዕቃዎች፣ (ጄኔሬተር፣ ሳውንድ ሲስተም፣ የኮምፒዩተር ጠረጴዛና ወዘተ …) ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0112 75 87 30/0118 95 97 88 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- በቂርቆስ ክ/ከተማ ት/ት ጽ/ቤት የሽመልስ ሀብቴ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የሠራተኞች የደንብ ልብሶች፣ አላቂ የቢሮ ዕቃዎች የጽዳት ዕቃዎችና ወዘተ … ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 551 94 13/011 551 94 13 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የአላጌ ግብርና ቴክኒክ ሙያ ት/ት ሥልጠና ኮሌጅ:: በጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልገው፡- የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች፣ የጽዳት ዕቃዎችና ወዘተ … ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 046 11 65 006/046

11 65 127 ይደውሉ::

ሽያጭ

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- ዕለት ደራሽ የዕርዳታ ትራንስፖርት:: በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ የሚፈልገው፡- ያገለገሉ ማርቸዲሲ ኢቪኮ ተሸከርካሪዎች እና ተሳቢዎች:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ታህሣሥ 11 ቀን 2005 ዓ.ም. ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0113 40 075/011 43 93 592 ይደውሉ::

------------------------------------

ኮንስትራክሽንጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- በደ/ብ/ብ/

ሕ/ክ/መንግሥት ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ የጉብርየ ዶሮ እርባታ ማዕከል /ጉራጌ ዞን/:: በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት የሚፈልገው፡- የቆሻሻ ማቃጠያ ቤት፣ መጋዘን፣ የመጸዳጃ ቤት ግንባታ:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 330 00 30/011 322 00 68/69 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- በቂርቆስ ክ/ከተማ ት/ት መምሪያ የአብዮት እርምጃ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት:: በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት የሚፈልገው፡- አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ የሠራተኞች የደንብ ልብስና ወዘተ … ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 551 07 65 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል:: በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት የሚፈልገው፡- የምግብ ማብሰያ ማዘጋጃ ህንፃ ግንባታ:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 022 225 02 10/11/16 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የቦሌ ክ/ከተማ አስተዳደር ቦሌ 17 ጤና ጣቢያ:: በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት የሚፈልገው፡- የሴራሚክስ የምንጣፍ፣

የማንሳትና የማስወገድ ሥራ፣ የመሬት ማስተካከልና አፈር የማንሳት ሥራ እና የካቢኔት ሥራ:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 6 62 80 43/0116 18 77 93ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የግብርና ምርት ማሣደጊያዎች አቅራቢ ድርጅት:: በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት የሚፈልገው፡- አሥፋልት:: ጨረታው የሚከፈተው፡- ታህሣሥ 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0114 40 04 58 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የኢትዮጵያ እህል ንግድ ድርጅት:: በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት የሚፈልገው፡- የቢሮና ሳይት ወርክ ሥራ:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0114 65 31 66/0114 66 47 43 ይደውሉ::

------------------------------------

ኪራይ ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- የቢንች

ማጂ ዞን ፋይ/ኢኮ/ልማ/ማስ/ዋና መምሪያ:: በጨረታ አወዳድሮ መከራየት የሚፈልገው፡- ዶዘር:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 047 335 05 76/047 335 08 67 ይደውሉ::

------------------------------------

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኤጀንሲ:: በጨረታ አወዳድሮ መከራየት የሚፈልገው፡- ሕንፃ:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 552 79 43 ይደውሉ::-

ጨረታውን ያወጣው መስሪያ ቤት፡- በአዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ የፕሮጀክት 14 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት:: በጨረታ አወዳድሮ መከራየት የሚፈልገው፡- የፕሪካስት ቢም የሚያጓጉዝ ትራንስፖርተሮች:: ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0118 96 16 52/0118 96 21 52 ይደውሉ::

------------------------------------

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያተ.ቁ. የሥራ መደብ ተፈላጊ የት/ደረጃና የሥራ ልምድ

1

የህግ አገልግሎት ኃላፊ/ቡድን መሪ

ከታወቀ ዩኒቨርስቲ በህግ የመጀመሪያ ዲግሪና የ5 ዓመት አግባብ ያለው የሥራ ልምድ

ደረጃ 19

ደመወዝ ብር 5,194

ብዛት 1 /አንድ/

አበል የኃላፊነት አበል ብር 400፣ የነዳጅ አበል 50 ሊትር ቤንዚን በወቅቱ የገበያ ዋጋ በገንዘብ ተለውጦ፣ የሞባይል አበል ብር 100

2

የሽቦ ስፊት ማሽን ኦፕሬተር

ከታወቀ ኮሌጅ/ የቴ/ሙያ ት/ቤት (10+1) በጠቅላላ መካኒክስ /ኤሌክትሪሲቲ ሙያ ሰርተፊኬትና የ2 ዓመት የሥራ ልምድ ወይም፣ 12ኛ ክፍል ወይም በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ 10ኛ ክፍል ያጠናቀቀና በሙያው 4 ዓመት የሥራ ልምድ

ደረጃ 8

ደመወዝ ብር 1,668

ብዛት 1 /አንድ/

የሥራ ቦታ አዲስ አበባ፣ የቅጥር ሁኔታ በቋሚነት፣ የሥራ ልምድ ከምረቃ በኋላ ሲሆን

መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ እስከ

10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ድረስ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃ ዋናውንና

የማይመለስ ፎቶኮፒና CV ከማመልከቻ ጋር በማያያዝ በድርጅቱ 7ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር

12 የሰው ሀብት ሥራ አመራር ቡድን ማመልከት የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-ለሁሉም የሥራ መደቦች 90% የህክምና ሽፋንለተ.ቁ. 2 ከመኖሪያ አካባቢ እስከ ድርጅቱ የደርሶ መልስ የትራንስፖርት አገልግሎት

ይሰጣል

የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት

CRYSTAL TANNERY SHARE COMPANY ክሪስታል ቆዳ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር

ክሪስታል ቆዳ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር፣ የባለ አክሲዮኖችን 4ኛ መደበኛ እና 1ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባዔ ጥሪ ክሪስታል ቆዳ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር፣ የባለአክሲዮኖች 4ኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ ቅዳሜ ታህሳስ 06 ቀን 2005 ዓ.ም፣ ከቃሊቲ የተሽከርካሪዎች ማሠልጠኛ ፊት ለፊት በሚገኘው የክርስቲያን በጐ አድራጐት (C.C.R.D.A) አዳራሽ ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ጀምሮ ያካሄዳል፡፡

የመደበኛ ጠቅላላ ጉባዔው አጀንዳዎች፡-1. የጉባዔውን ረቂቅ አጀንዳ መርምሮ ማፅደቅ፣2. የዳይሬክተሮች ቦርድ የ2004 ዓ.ም ዓመታዊ ሪፖርት ማዳመጥና ተወያይቶ

መወሰን፣3. የ2004 ዓ.ም የሥራ ዘመን የውጭ ኦዲተሮች ሪፖርት ማዳመጥና ተወያይቶ

መወሰን፣4. ክፍያውን አጠናቀው ያልከፈሉ ባለአክሲዮኖችን በተመለከተ ተወያይቶ መወሰን፣5. ሌሎች፣

የድንገተኛ ጉባዔው አጀንዳዎች፡- 1. የጉባዔው ረቂቅ አጀንዳ ማፅደቅ፣ 2. አዲስ አባላትን መቀበል፣3. የዳሬክተሮች ቦርድን ሥልጣንና ተግባር ማሻሻል፣4. ሌሎች፣

ማሳሰቢያበጉባዔው ላይ መገኘት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች፣ ጉባዔው ከሚካሄድበት ቀን በፊት፣ ቦሌ ፍሬንድ ሺፕ ህንፃ 4ኛ ፎቅ፣ ቢሮ ቁጥር 408 በሚገኘው የአክሲዮን ማህበሩ ጽ/ቤት በመገኘት የውክልና ቅጽ በመሙላት ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን በተሰጠው አካል ፊት የተሰጠ በስብሰባው ለመገኘት ድምጽ ለመስጠት የሚያስችል ውክልና፣ ዋናውንና አንድ ፎቶ ኮፒ በጉባዔው ዕለት ይዞ በመቅረብ መሳተፍ ይችላሉ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥሮች 251-118-60-17-82 251-011-4-34-87-35 ክሪስታል ቆዳ ፋብሪካ አክሲዮን ማህበር የዳይሬክተሮች ቦርድ

Page 15: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 15 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ሪፖርተር፡- በአሁኑ ጊዜ የውጭ አገር የሥራ ስምሪት አገልግሎት ሰጭ ኤጀንሲዎች የሥራ እንቅስቃሴ በምን ሁኔታ ላይ ይገኛል?

አቶ መዝገቡ፡- በአሁኑ ሰዓት ያለው የኤጀንሲዎች እንቅስቃሴ ቀደም ካሉት ጊዜያት ማለትም ከረመዳን በፊት ከነበረው ሁኔታ ጋር አንፃር ሲታይ በጣም የተቀዛቀዘና የተዳከመ ነው:: ምክንያቱ ደግሞ በተቀባይ አገር ያሉ አሠራሮች ናቸው:: በአንድ በኩል ወቅቱ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ከኢትዮጵያ ወደ ተቀባይ አገሮች የሚላኩ የቤት ሠራተኞችን በፍጥነትና በተቀላጠፈ መልኩ አለመላክ በመኖሩ ነው:: ሌላውና በዋናነት ልንጠቅሰው የምንችለው ነገር ቢኖር የሰዎች ዝውውር ሕገወጥነትን የተከተለ መሆኑም ጭምር ነው:: በዚህ መሠረት ሕጋዊው አሠራር እየተዳከመ ሊመጣ ችሏል:: ምናልባት በሂደት ይሻሻላል ብለን እንጠብቃለን::

ሪፖርተር፡- በአሁኑ ጊዜ ከኢትዮጵያ የቤት ሠራተኞችንም ሆነ በሌላ ሙያ የሚወስዱ አገሮች ምን ያህል ናቸው?

አቶ መዝገቡ፡- በአሁኑ ጊዜ በሕጋዊ መንገድ ሠራተኞችን እየተቀበሉ ያሉትና መላክም የሚቻለው ሳዑዲ ዓረቢያና ኩዌት ብቻ ነው:: ወደኩዌት የሚሄደው ሠራተኛ ቁጥር በጣም ቀንሷል:: ምክንያቱም ደግሞ ሠራተኞቹ በሕገወጥ መንገድ ስለሚሄዱ ነው:: በተጨባጭ በኢትዮጵያ የኩዌት ኤምባሲ ከሚሠሩ የበታች ሠራተኞች ጋር በሚደረግ የምስጢር ግንኙነት ሕገወጦችን የሚያበረታታ በመሆኑና ከተጠያቂነትም ለማምለጥ ሲሉ ቀጣሪዎችም ሕገወጥ አሠራሩን በመምረጣቸው ሕጋዊ ሥርዓቱን በሚቃረን መልኩ እየተሠራ ነው:: በመሆኑም ሕጋዊዎቹ ኤጀንሲዎች ሥራቸው እየተዳከመ ነው:: በየቀኑ ወደኩዌት የሚገባው እጅግ በጣም ብዙ ቢሆንም ከሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጸድቆለትና ሕጋዊ መንገዱን ተከትሎ የሚሄደው ግን እጅግ በጣም ትንሽ ነው:: ይኽ ሁኔታ የሚያሳየው ግን ሕግ እየተጣሰ በሕጋዊ መንገድ በሚላከው ቪዛ ዜጎች በሕገወጥ መንገድ እየሄዱ ነው::

ሪፖርተር፡- ምክንያቱ ምንድነው?

አቶ መዝገቡ፡- የዚህ ምክንያት ብዙ ነው:: አንዱና ዋነኛው ቁጥጥሩና ክትትሉ በአግባቡ አለመቃኘቱ ነው:: ዜጎች በየትኛውም ቦታ የመዘዋወር ሕገመንግሥታዊ መብት አላቸው:: ነገር ግን በተለይ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ የሚደረገው ጉዞ ለሥራ መሆኑን መንግሥት ጠንቅቆ ያውቃል:: ጉዞው የሚደረገው በአዋጅ ቁጥር 632/2001 መሠረት ተግባራዊ መሆን ሲገባው፣ ዜጎች በተለያየ መንገድ የሚመጣላቸውን ቪዛ ሕጋዊ ሳያስደርጉና ሳይመዘገቡ ዝም ብለው ነው የሚሄዱት:: ይኽ ደግሞ በውጭ አገር ያሉ ሕገወጦች ቪዛዎችን እያወጡ ወደ ኢትዮጵያ ሲልኩ እዚህ ያሉት ሕገወጦች ተቀብለውና በሕገወጥ መንገድ ለመለመሏቸው ዜጎች ይሰጣሉ:: በዚህ መካከል ሕገወጦቹ እየተጠቀሙባቸው ይገኛሉ:: የሚሄዱት በተለይ ዕድሜያቸው ዝቅተኛ የሆኑ ወጣቶች ኢንሹራንስ ይኑራቸው አይኑራቸው ስለማያውቁ በሄዱበት አገር አደጋ ሲደርስባቸው የማይታወቅበት መልክ ብዙ ነው:: የት እንዳሉና ማን እንደቀጠራቸው፣ በስንት እንደተቀጠሩ፣ ቀጣሪዎች ለሕገወጦች ከፍለናል የሚሉት ገንዘብ ስንት እንደሆነና ከሄዱ ከስንት ጊዜ በኋላ ደመወዛቸውን እንደሚያገኙ አይታወቅም:: ዜጎች ወዴት እንደሚሄዱና ለምን እንደሚሄዱ እነሱ ብቻ ሳይሆኑ መንግሥት ራሱ ማወቅ አለበት:: መንግሥት ዜጎቹን የመመዝገብና የማወቅ ግዴታ አለበት:: መንግሥት በየኬላው ተቆጣጣሪ አቁሞ መቆጣጠሩ ቀርቶ በአየር መንገድ የሚወጡትንም መቆጣጠር አቅቶት ይታያል:: በዚህ የተነሳ ዜጎች በተለያዩ መንገዶች በሕገወጥ መንገድ እየወጡ ነው:: የሚደርስባቸውን አደጋ ደግሞ እኛ ከኤጄንሲዎች በበለጠ ሞተው አስከሬናቸውና ጉዳት ደርሶባቸው የሚመጡት በአየር መንገድ በኩል በመሆኑ መንግሥት ጠንቅቆ ያውቀዋል::

ሪፖርተር፡- እንደ ማኅበር ኤጀንሲዎች የሚልኳቸውን ዜጎች ደህንነት ባንድም በሌላም የማወቅ አጋጣሚ ይኖራችኋል፤ ለሥራ የሚወጡ ዜጎች ላይ የሚደርሰው የሞት፣ የአካል መጉደልና የሠሩበትን ደመወዝ መነጠቅስ እንዴት ነው?

አቶ መዝገቡ፡- በሕጋዊ መንገድ በኤጀንሲዎች በኩል የሚሄዱት ዜጎች ሁኔታ ይታወቃል:: ሕጋዊ

‹‹ወደ ዓረብ አገሮች የሚሄዱ ዜጎችን ሕይወት ለመታደግ የመንግሥት ዕርዳታ አስፈላጊ ነው››

አቶ መዝገቡ አሰፋ፣ የአሠሪ ኤጀንሲዎች ፕሬዚዳንት

ማንም ሰው በፈለገበት ቦታና አገር የመዘዋወር መብቱ በሕገ መንግሥቱ ተረጋግጦለታል፡፡ ይኽንንም ታሳቢ በማድረግ በሰዎች የመዘዋወርና የመሥራት መብቶች ዙሪያ ብዙም ችግሮች አይታዩም፡፡ ቁጥጥር አለመደረጉ ግን በነፃነት ከመዘዋወር ጋር ተያይዞ ችግሮች አይደርሱም ማለት አይደለም፡፡ ለዚህም በዋነኛነት ማሳያ የሚሆነው በተለያዩ የዓረብ አገሮች በቤት ሠራተኛነት በሚሄዱት እህቶቻችን ላይ እየደረሰ የሚታየው የሞት፣ የአካል መጉደል፣ የመደፈርና ያለደመወዝ ማባረር ጥቂቶች ናቸው፡፡ የነዚህ ዜጎች እንግልት የሚጀምረው አገራቸው ላይ ነው፡፡ ከተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች በደላላዎች

ተመልምለው አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ፓስፖርት እስከሚያወጡና የሕክምና ምርመራ እስከሚደረግላቸው ድረስ ብዙ ችግሮችን ያሳልፋሉ፡፡ ሁሉም ነገር ተሳክቶላቸው እስከሚሄዱ ድረስ የደላሎቹ የወሲብ መፈጸሚያ ይሆናሉ፡፡ ተመርምረው ውጤታቸው ተበላሽቷል ተብለው ወደመጡበት እንዲመለሱ ሲነገራቸው እንደ ውርደት ስለሚቆጥሩት ተመልሰው ወደቀያቸው መግባትን ይተዉና ራሳቸውን በመሸጥ

ለመተዳደር ይሞክራሉ፡፡ ብዙ ብዙ ችግሮች ውስጥ ይገባሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ያለውን ወደ ዓረብ አገሮች የሚሄዱ ሴቶች ዕጣ ፈንታ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ እንዲገልጹልን አቶ መዝገቡ አሰፋ የኢትዮጵያ የውጭ ሥራ ስምሪት አገልግሎት ሰጭ ኤጀንሲዎች አሠሪ ማኅበር ፕሬዚዳንትን ታምሩ ጽጌ አነጋግሯቸዋል፡፡

መንገድን ተከትሎ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ተረጋግጦና ተጣርቶ ስለሚላኩ በነሱ በኩል የሚደርስ ችግር ብዙም የለም:: በሕመም፣ በተፈጥሮ ሞትና በተለያዩ ምክንያቶች የሚደርሰው ችግር እንደተጠበቀ ሆኖ ቢያንስ ቢያንስ ከሕገወጥ ጉዞው የተሻለ ሁኔታ ላይ ነው:: በምንም ይሁን በምን አደጋ ሲደርስባቸው የመከታተልና በአግባቡ ወደአገራቸው መመለሱ ግዴታም ነው:: የተጎጂ ቤተሰቦችም ተጠቃሚ የሚሆኑበት ኢንሹራንስ አለ:: በሕጋዊ መንገድ የሄዱ ዜጎች በተፈጥሮ፣ ባለማወቅ ወይም ሆን ተብሎም ቢሆን ለሚደርስባቸው ጉዳት ሕጋዊ የሆነና ተጠሪ የሆነ ኤጀንሲ አለ:: መንግሥት ኅብረተሰቡና ቤተሰብ የሚያውቁበት ሕጋዊ አሠራር አለ:: ሕገወጡ ፍልሰት ግን ተቀባይነት ማጣቱ ብቻ ሳይሆን ዜጎቹም፣ ቤተሰቦቻቸውም ተጎጂዎች ናቸው::

ሪፖርተር፡- በመረጃ ደረጃ እናንተ የተሻለ ዕውቀት አላችሁ:: በየቀኑ ሞተው የሚመለሱና ተጎድተው የሚመጡ ዜጎች እንዳሉ ሲነገር እንደነበር ይታወቃል:: በአሁኑ ጊዜ ያለበት ደረጃ ምን ይመስላል?

አቶ መዝገቡ፡- እውነት ለመናገር በአሁኑ ጊዜ ከፎቅ ተወርውራ፣ ውኃ ተደፍቶባት፣ ተገፍትራ ወዘተ የሚባለው ነገር በጣም ቀንሷል:: ነገር ግን በሕጋዊ መንገድም ሄደው አንዳንድ ጊዜ የሥራ ባህሉን ካለመላመድና ካለመቻል የተነሳ ችግሮች ያጋጥማቸዋል:: ምክንያቱ ደግሞ በቂ ዝግጅትና ልምድ ሳይዙ ስለሚሄዱ ነው:: ለነገሮች ሁሉ አዲስ ከመሆን ጋር ተያይዞ የሥነ ልቦና ችግር በብዛት ይደርስባቸዋል:: እኛ እንደማኅበር ደጋግመን መናገር የምንፈልገው በአዋጁ መሠረት በቂ ሥልጠናና ግንዛቤ አግኝተው መሄድ አለባቸው::

ሪፖርተር፡- ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ወደ ውጭ በሚላኩ ዜጎች ዙሪያ ትኩረት ሰጥተው መሥራት ያለባቸው የትኞቹ ናቸው?

አቶ መዝገቡ፡- አዋጁን በተግባር ላይ ማዋል ያለበትና መከታተል ያለበት ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው:: እሱ ደግሞ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሆኖ ሥርዓተ ትምህርት በመቅረጽ ቢያንስ ቢያንስ ዝቅተኛ የሆነው ዕውቀት አግኝተው እንዲሄዱ ለማድረግ የመሥራት ኃላፊነት አለበት:: ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት በቲቪቲም ይሁን ወይም ባለሀብቶችም ገብተውበት የሥልጠናውን መንገድ በማመቻቸት ዜጎችን ማብቃት አለባቸው:: ይኸንን ኃላፊነት መውሰድ ያለበት ደግሞ ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው::

ሪፖርተር፡- አጭርና ሁሉን ያካተተ ሥልጠና መጀመሩን ሚኒስቴሩ ሲናገር ቆይቷል:: አልተጀመረም እንዴ?

አቶ መዝገቡ፡- ይነገረናል፤ ግን መቼ ተግባራዊ እንደሚሆን አናውቅም:: በሚኒስቴሩ የውጭ ሥራ ስምሪት ዳይሬክቶሬት ባንድ ወቅት በመገናኛ ብዙሀን በቅርቡ እንደሚጀመር ሲናገሩ ሰምቻለሁ:: ከዛም በፊት ሲነገር ነበር፤ ካልተጋነነ ዓመት አልፎታል:: በዚህ ጉዳይ ብዙዎች ለኪሳራ ተዳርገዋል የሚመለከተው አካል አሁንም ዛሬ ነገ ሳይል ወደ መሬት አውርዶ መጀመር አለበት:: ምናልባት ሲማሩና ሲረዱት ሐሳባቸውን ቀይረው አገራቸው ላይ የሚሠሩበትን አማራጭ ሊወስዱ ስለሚችሉ ጥቅሙ ብዙ ነው:: ለማመዛዘን ይረዳቸዋል:: ከሌሎች አገሮችም ጋር ተወዳዳሪ ሆነን ዛሬ በዝቅተኛ ግምት 180 ዶላር የሚሉትን፣ 250 እና 300 ዶላር የማናደርግበት ሁኔታ የለም:: ከዮርዳኖስ ጋር ባደረግነው ውል፣ ልምድ ያላቸውንና በቀላሉ ካሠሪዎቻቸው ጋር መግባባት የሚችሉትን በ230 ዶላር ነው የተፈራረምነው:: ልምድ የሌላቸውን ደግሞ 200 ዶላር አድርገናል:: ይኸ የሚያሳየው ኢትዮጵያውያን ተፈላጊ መሆናቸውን ነው:: ሠልጥነውና አውቀው ቢሄዱ ደግሞ የበለጠ ተፈላጊነታቸው ይጨምራል:: ስለዚህ ለዜጎች ደህንነትና ከሄዱ አይቀር ተገቢ የሆነ ክፍያ እንዲያገኙ ሥልጠናው ቢሰጣቸው ተገቢ በመሆኑ የሚመለከተው አካል ከሌሎቹ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሥልጠናውን ባፋጣኝ ቢጀምረው የተሻለ መሆኑን እንመክራለን::

ሪፖርተር፡- ኢሚግሬሽን አካባቢ ለሥራ ያልደረሱና በጣም ወጣት ልጆች ፓስፖርት ለማውጣት ተሰልፈው ይታያሉ:: ለምን እንደመጡና እንዴት እንደሚሄዱ ሲጠየቁ በኤጀንሲዎች በኩል እንደሚሄዱ ይናገራሉ:: በሕገወጥ መንገድ የሚሠሩ ኤጀንሲዎች አሉ?

አቶ መዝገቡ፡- ይኖራሉ:: ምንም ጥርጥር የለውም:: ከኢሚግሬሽንና ዕድሜ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጥያቄ ብዙ ነው:: ችግሩ ከክልል ይጀምራል:: ከታችኛው የመንግሥት መዋቅር ማለትም ከወረዳ ይጀምራል:: ዕድሜያቸው እንዳልሞላ እየታወቀ የ15 ዓመትን ልጅ 23 ብለው ይሰጣሉ:: በቀላሉ ከአካባቢ በማጣራትና አይቶም መገመት ሲቻል ምክንያቱ በማይታወቅ ሁኔታ ከፍ አድርገው ይሰጧቸዋል:: በአሁኑ ጊዜ አዲስ አበባ ላይ እየመለሷቸው ነው የሚል መረጃ አለኝ:: በተለይ ድሬዳዋና ጅማ ላይ እየተሰጠ ያለው የሚያስደነግጥ ነው:: እኛ መረጃው በእጃችን አለ:: ከልጆቹ በተለያየ መልኩ ባደረግነው ማጣራት ያገኘነው መረጃ በእጃችን ይገኛል:: በአሁኑ ጊዜ በተለይ ከወሎ አካባቢ በቀጥታ ወደ ድሬዳዋ እየፈለሱ ነው:: በጣም ትናንሽ ልጆች:: ያለምንም ሥልጠና ልከን ለሞትና ለአካል መጉደል ከምንዳርጋቸው የሚመለከተው አካል ክትትል በማድረግ በእንጭጩ መቅጨቱ የተሻለ ነው እንላለን:: በአሁኑ ጊዜ ወደ ሳዑዲና ኩዌት ለመሄድ የሚመጡት መጻፍ፣

ማንበብ የማይችሉና ፎቶግራፋቸውንና የወረቀቱ መጠን በማየት መታወቂያና ፓስፖርት መሆኑን መለየት የማይችሉ ናቸው:: ማንም ሰው ወደ ኢምግሬሽን ቢሄድ በቀላሉ መረዳት ይችላል:: ሁሉም የኅብረተሰብ አካል ሊቆጣጠራቸው ይገባል:: በደላላ የሚመጣን ቪዛ ተመልክቶ መላክ ከባድ ወንጀል ከመሥራት ተለይቶ አይታይም::

ሪፖርተር፡- ለዚህ አሠራር ዋናው ተጠያቂ ማነው?

አቶ መዝገቡ፡- ዋናውና ትልቁ ተጠያቂ ቤተሰብ ነው:: ቤተሰብ ራሱ እንዲሄዱ በመገፋፋት ብዙዎችን ለብዙ አደጋ ያጋለጠው ቤተሰብ ነው:: በእርግጥ ያለ መመቻቸትና የኑሮ ሁኔታ ሊኖር ይችላል:: ግን ልጆቻችንን በመላክ ኑሯችንን ለመደጎም የምናደርገው ዝንባሌ፣ ልጆቹን ወደ ውጭ እንዲሄዱ እየገፋፋቸው ነው:: ሌላው ተጠያቂ ደግሞ ደላላው ነው:: በውሸት ፕሮፓጋንዳ በየቀያቸው እየሄደና እየሰበከ ዜጎችን ለጉዳት እየዳረጋቸው ነው:: ሁሉም ነገር አልጋ ባልጋ እንደሆነና ወርቅ ተነጥፎ እንደሚጠብቃቸው አስመስሎ በመስበክ ዜጎችን እያስጨረሰ ነው:: ኅብረተሰቡ ይኸንን እንዲገነዘብ የማድረግ ሥራ ደግሞ የመንግሥት ነው:: ይኽንን ባለማድረጉ መንግሥት ዜጎችን ከመጠበቅና ካለበት ኃላፊነት አንጻር እሱም ተጠያቂ ነው:: የሥራ ዕድሉ ካለ በማንኛውም መልኩ አገር ውስጥ መሥራት ይመረጣል:: ይኽንን ደግሞ ማመቻቸት ያለበት መንግሥት ነው:: መሄድ ካለባቸው ሕጉንና ሕጉን ብቻ ተከትለው እንዲሄዱ መንግሥት በሚመለከተው ተቋም በኩል ሕዝቡን ማሳወቅ አለበት:: በትምህርት ቤት፣ በሃይማኖት ተቋማት፣ ከላይ እስከ ታችኛው ወረዳ ድረስ በመንቀሳቀስ የማሳወቅ ሥራ መሥራት አለበት:: በተለይ ከገጠር አካባቢ የሚመጡት የሚያምኑት ደላላን ብቻ ስለሆነ መንግሥት ጠበቅ ያለ ዕርምጃ መውሰድ አለበት:: ደላሎች ከየክፍለ ሀገሩ ሰብስበው በማምጣት አዲስ አበባ ተከራይተው ያስቀምጧቸዋል:: ቪዛው ሲላክላቸው ይልኳቸዋል:: እስከዛ ድረስ ከማንም ጋር እንዲገናኙ አይፈቀድላቸውም:: በዚህ መልኩ ዜጎች ለክፉ ነገር እየተጋለጡ በመሆኑ መንግሥት ሊያስብበት ይገባል:: ከሕጋዊ ኤጀንሲዎች ጋር እንዲሠሩ ማድረግ ነው:: ግብር እንዲከፍሉ ማድረግ ተገቢ ነው:: ኤጀንሲዎችም ከማኅበሩ ማረጋገጫ ካልተሰጣቸው መቀበል የለባቸውም:: በአካል ሳይገኙ የሚሞላው ፎርም እንዲቀርና ለመሄድ የሚፈልጉትን ተሞልቶ የመጣውን ሰነድ መቀበል ብቻ ሳይሆን መልካቸውን ማየት ወሳኝ ነው:: ከዚህ ሲሄዱ በቀን ስምንት ሰዓት ለመሥራት ነው:: እውነቱ ግን የተገላቢጦሽ ነው:: በሥልጠና ላይ ይኽንን በደንብ ማስረዳትም ያስፈልጋል::

ሪፖርተር፡- አብዛኛዎቹ ተመልምለው የሚመጡት ከክልሎች ነው:: እናንተ እንደ ማኅበር ከክልልና ከፌዴራል ኃላፊዎች ጋር ውይይት በማድረግ ችግሩ የሚቀንስበትን መንገድ ለመፈለግ አልሞከራችሁም?

አቶ መዝገቡ፡- በተለያዩ አካባቢዎች በሚደረጉ ውይይቶች ላይ የማኅበሩ ተወካዮች እየተገኙ ያለውን ችግር ለማስረዳት ተሞክሯል:: በቅርቡ በኮምቦልቻ የተደረገውን ውይይት ለአብነት ለመጥቀስ ይቻላል:: በመገናኛ ብዙኃንም ከሚመለከታቸው ኃላፊዎች ጋር በመሆንም ውይይት አድርገናል:: ነገር ግን አሁንም ቢሆን ብዙ ያልሠራናቸው ነገሮች አሉ:: ለመሥራት ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት ላይ እንገኛለን:: ፕሮፌሽናል የሆኑ ባለሙያዎችን አካተን በሁሉም ክልሎች በሚገኙ መገናኛ ብዙኃን፣ ጋዜጦችና መጽሔቶች የማኅበሩን ዓላማ ማስተዋወቅና ዜጎች ወደ ውጭ ለመሄድና ለመሥራት ከፈለጉ በሕጋዊ መንገድ ቢሄዱ የሚያገኙትን ጥቅም፣ ሕገወጥ በሆነ መንገድ ከሄዱ የሚደርስባቸውን ጉዳት በማሳወቅ ዜጎችን ከጉዳት ለማዳን በዝግጅት ላይ እንገኛለን:: ከተቀባይ አገሮች ጋር ካሉ አቻ ማኅበሮችና ድርጅቶች ጋር በመነጋገር ከላክናቸው በኋላ የሚደርስባቸውን ችግር ለመቀነስና ለማስወገድ ሰፊ ጥረት እያደረግን ነው::

ሪፖርተር፡- የሚመለከታቸው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በዜጎች ላይ እየደረሰ ስላለው ጉዳት የሚሰጡት ምላሽ ምንድነው? ብዙ ጊዜ በመገናኛ ብዙኃን ሲነገር እንደሚሰማው ባደረጉት ጥናት የሚደርስባቸውን ጉዳት ሲገልጹ የሚሰሙ መሥሪያ ቤቶችና ጥናት አቅራቢዎች ሲናገሩ ይሰማሉ:: ምን ያህል ውጤት አስገኝተዋል?

አቶ መዝገቡ፡- ምን ያህል ውጤት ተገኝቷል ወደ ገጽ 42 ዞሯል

Page 16: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 16|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

ማስታ

ወቂያ

z ¡ Wüእነሆ ዛሬ የምንጓዘው ከ22 ወደ ካዛንቺስ ነው። የሜዳ ላይ ቸርቻሪው ዕቃውን ከፍ አድርጎ

እያሳየ ዋጋውን ጮክ ብሎ ይጣራል። መንገደኛው መለስ እያለ የዕቃውን ዓይነት ይቃኛል። ‹‹ስሚ! እኔ አንቺን አጥቼ ምንም አልሆንም እሺ? ገንዘብ አያሳጣኝ እንጂ፤›› ይላል ቲሸርትና ካልሲ የሚሸጠው የጎዳና ላይ ቸርቻሪ። ሰዎች ‹‹ማንን ይሆን?›› እያሉ ከቀኝ ወደ ግራ ከኋላ ወደ ፊት እየተገላመጡ የምትሸኘዋን ሴት ለማየት ይቃብዛሉ። ሁኔታውን እያዩ ከሚስቁትና ‹‹ሙድ›› ከሚይዙት ሦስት ወጣቶች አንደኛው “ካዛንቺስ! ካዛንቺስ!” ብሎ ድንገት ጮኸና አጠገቡ የቆመችውን ታክሲ ጠቆመ። ‹‹ጩኸት እንኳ በአቅሙ እንደ ብራ መብረቅ እንዲህ ካስደነገጠን ኑክሌር ቢሆን ኖሮ እስቲ አስበው፤›› ብላኝ ጠየም ያለች ፍልቅልቅ ልጅ ታክሲው ላይ ተሳፈረች። ‹‹ገዳማ ገደምዳማዬ፣ ያችን ጠይም ወጣት አያችሁ ወይ›› ያለው ዘፋኝ ወዶ አይደለም ለካ? ተከትያት ገባሁና ከልጅቷ ጎን ተቀመጥኩ። ውበት ስናሳድድ የሕይወት ኮምፓሳችን ወዴት አቅጣጫ እንደሚወስደን በማሰብ ‹‹ወይ ዘመን?›› እያልኩ ማጉተምተም ጀመርኩ። ልጅቷ ሰማችኝ መሰል ሰው ሁሉ ወይ ዘመን ሲል ነው የምሰማው፤›› ብላ ዓይኔን ዓይን እያየች መልስ ትጠብቅ ጀመር። የመቶ ብር ኖት ሰጥታኝ መልሷን የከለከልኩ ወያላ አስመስላኝ አረፈችው። ‹‹አይ! ኑክሌር እስኪፈነዳ ምን አስጠበቀን? ኑሮ ራሱ ከኑክሌር ብሶ ፈንድቶ የለም ወይ ለማለት ነው፤›› ብያት አፌን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ዘጋሁ። ዘንድሮ የዕድገትና የትራንፎርሜሽን ዕቅዱን ወሬ የሚያስፈጽመው ይመስል ከአፍ ከአፋችን የምንለውን የሚለቅሙ አልበዙባችሁም?

በወያላው ጩኸት አንዳንዱ ሳያስበው ሌላው ደግሞ እንዳሰበው ይሳፈራል። ወያላው ወዲያው መጣራቱን ለአፍታ አቁሞ ‹‹ምን አድርጋህ ነው እንዲህ ጎዳና ላይ የምታሰናብታት?›› ይለዋል ቸርቻሪውን። እንዲህ በአጋጣሚ የሚለያየውን ጎዳና ይቁጠረው። በጫት ጉንጩ የተወጠረው ቸርቻሪ፣ ‹‹ምርጥ ምርጥ ካልሲ በአምስት ብር›› ሲል ቆየና ወደ ወያላው መለስ ብሎ፣ ‹‹የድፍረቷ ድፍረት ዛሬ እስኪ ምሳ እዚህ አካባቢ አንድ ምግብ ቤት ገብተን እንብላ አትለኝ መሰለህ? ገንዘቤን ልበላው ካልሆነ በስተቀር ምግብ ልበላበት እንደማልችል አውቀዋለሁ፤›› ሲለው መንገደኛውን ሳይቀር ፈገግ አሰኘው። ‹‹ታዲያ ወዴት ሸኘሃት?›› አለው ወያላው ጨዋታውን እንደ መዝናኛ ቆጥሮ። ‹‹እንጃ! መሄጃ ይጠፋል ብለህ ነው? ያውም ቆንጆ ፈላጊ እንዲህ በሞላበት ዘመን፤›› ሲል ታክሲው ውስጥ የተሳፈረ አንድ ጎልማሳ፣ ‹‹እውነት ነው። ሳስበው የልማት ፖሊሲያችን ለእህቶቻችን ማበብና መፍካት የሚያደላ ይመስለኛል። ገንዘብ ዋጋ ሲያጣ ቁንጅና ከመጠን በላይ እየሆነ መጣ እኮ፤›› አለና እየሳቀ ተመቻችቶ ተቀመጠ። አጠገቤ ያለችዋ ተሳፋሪ፣ ‹‹አቤት ኮምፔሌክስ! መቼም ዘንድሮ የማይቀናበት ነገር የለም። ደግሞ ብላችሁ ብላችሁ መንግሥት ለብቻችሁ የቀረፀላችሁ የልማት ፖሊሲ አለ ልትሉን ነው? ፀሐዩ መንግሥታችን እኩልነታችንን አረጋግጦ አንገታችን ቀና ቢያደርግልንም የጓዳችን ጉድለት እኮ እኩል ነው፤›› ብላ እሷም ብቻዋን ሳቀች። በቀላሉ የማትላቀቀው ሙግት ውስጥ እየገባች መሆኑን ልብ አላለችውም። ልብ የማንለው ስንቱን ይሆን!

ታክሲያችን መንቀሳቀስ ጀመረች። ወያላው ገብቶ በሩን እየዘጋ ሾፌሩን ስለ ቸርቻሪውና ፍቅረኛው ወሬ መዘገብ ጀምሯል። አሁንም ሲናገር በጩኸት ነው። መስማታችን ላይቀር አንዳንዶች ለምን ረጋ ብለው እንደማይናገሩን አይገባንም። ‹‹የዘንድሮ ነጋዴ እኛ ውለን እንግባለት እንጂ የትስ ከፍሎ ቢበላ ምን ያሳስበዋል?›› አለው ሾፌሩ ቸኮል ቸኮል እያለ ቀበቶውን እያሰረ። ‹‹ተው! ተው! መጀመሪያ ሒሳቤን ልቀበልና ከዚያ እንደፈለግክ አውራ። ስንት ነጋዴ እንደተሳፈረ ምን ታውቃለህ?›› ብሎት እየሳቀ ወደ እኛ ዞረ። በትንሽ በትልቁ የሚቀያየመውን በቀላሉ ለማወቅ የረጅም ጊዜ ወያላነቱ ልምድ ያገዘው ይመስላል። ጎልማሳውና አጠገቤ የተቀመጠችው ጠይሟ ቆንጆ ሙግታቸውን እያሟሟቁ ነው። ‹‹ኧረ ሴቶች እበካችሁ ተውን ተው!? ተራቆትንላችሁ እኮ! እናንተ ማማር አይታክታችሁ እኛ በስጦታ ማንበሽበሽ አይታክተን፤›› ሲል አጠገቡ የተቀመጠ ተሳፋሪ፣ ‹‹እኩልነት እኩልነት ያላችሁት በሚሰጣችሁ ዕድል እንድትሠሩና ያቅማችሁን ለአገርና ለወገን እንድትጠቅሙ መስሎን ነበር። ነገር ግን…›› ብሎ ተወው። ቆንጂት በበኩሏ፣ ‹‹እናንተስ ሥራ ፈታችሁ ስለኛም ስለሌላውም ወሬ በማውራታችሁ አይደል አንድ ዓይነት አስተያየት ብቻ የምትሰጡን?›› ብላ በፈገግታ መለሰችላቸው። ፈገግታዋ ዓይናችንን አፈዘዘው። ‹‹ፊታቸው የማይፈታ ባለሥልጣናት አጋቡብን መሰለኝ ኮስታራው እየበዛ ነው፤›› ይላል አንዱ ድንገት ጥልቅ ብሎ። ያለውን ቢል ለምን አልክ ማለት ድሮ ቀርቷል። ዘመኑ ሐሳብ በነፃነት እንዲገለጽ የሚፈለግበት ነዋ!

ወያላው ሒሳቡን እየተቀበለ ሾፌሩን፣ ‹‹ኧረ ንዳው ኳስ ይጀመራል እኮ፤›› ይለዋል። ጠና ያሉ ተሳፋሪ ደግሞ፣ ‹‹ዘንድሮ ለሥራ የሚቸኩል ሰው አላይ አልን በቃ? ቀስ በል ሾፌር። ከሕይወታችንና ከኳስ የቱ ይበልጣል?›› ብለው ወያላውን እያዩ ጠየቁት። ‹‹አይ አባት ማን በዚህ ጊዜ ለነፍሱ ይኖራል ብለው ነው?›› ብሎ መልሶ ቢጠይቃቸው እንቆቅልሽ ሆነባቸው መሰል፣ ‹‹እንዴት? እንዴት?›› አሉት መልሰው። ‹‹አቤት የዘንድሮ ልጅና ንግግሩ፣ ምንም አያውቁም ትባላላችሁ ግን ውስጠ ወይራ ንግግራችሁ ውስጡን ለቄስ ነው፤›› ብለው ሽሙጡን እያዳናቁ እንዲያብራራላቸው ጠየቁት። ‹‹ያው በቃ ኑሮ ከላይ ከላይ ብቻ ነው የሚያስጋልበን ለማለት ነው። ለቁሳቁስ፣ ለብልጭልጭ፣ ለእለት ፍጆታ፣ ወዘተ እንጂ ነፍስን መቼ አስበናት? የመኖርን ዓላማ መቼ አገናዝበነው ነው ብለው ነው?›› ካላቸው በኋላ የሰጡትን አሥር ብር ዘርዝሮ መልስ እየሰጠ፣ ‹‹ለነፍስ እንኑር ብንልማ ስንቱ መሰለዎት ዕድሜው ወደ ኋላ እንደ ሰዓት ሊሞላለት ግድ የሚለው፤›› ቢላቸው የአንደበቱና የአስተሳሰቡ ስልነት ደንቋቸው ተመለከቱት። ሁላችንም ስለነፍሳችን ጥሪ፣ ስለሞራል፣ ስለማንነት፣ ወዘተ በማሰብ ተወዘወዝን። የኑሮ አባዜ ጎዳናው ላይ ሰውን በሩጫ ሲወዘውዘው እያየን ወደነበርንበት ባንመለስ ደግሞ የት በደረስን ነበር፡፡

ወያላው ሥራውን ጨራርሶ ተቀምጧል። አንዳንድ ወጣቶች አዛውንቱና ወያላው ባነሱት ጨዋታ ተነስተው ስለመሆንና አለመሆን መጨዋወት ጀመረዋል። ‹‹ወይኔ እኔ መቼ አወቅኩ ይኼን ሁሉ፤›› ይለዋል አንደኛው። ‹‹እንዴት?›› ሲለው መልሶ አዳማጩ፣ ‹‹ያኔ ጠቀም ያለ ገንዘብ ያስቆጥራል ብለውኝ ገብቼ ተምሬ አሁን ፈጽሞ ሥራዬን ልወደው አልቻልኩም፤›› ይለዋል። ‹‹ታዲያ ለምን ሥራውን ትተህ ራስህን አታዳምጥም?› እያለ ሲጠይቀው የታክሲዋ ጣራ የሚሰነጠቅ እስኪመስል ድረስ እየጮኸ ነበር፡፡ ወያላውም እንደ ቤተ መጻሕፍት አስተናባሪ ‹‹ፀጥታ ይከበር›› ብሎ ታክሲዋ ውስጥ የሚለጥፍ እስኪመስል ድረስ ተንከትክቶ ሳቀ። ‹‹ምን ያስቅሃል?›› አለው አቋርጦት። ትዝብቱ በሳቁ መሀል ኃፍረትንና መረታትን ያሳያል። ‹‹ወዳጄ! ለመሆኑ የዚህ አገር ነዋሪ ነህ? ራስን ማዳመጥ እኮ ሙዚቃ አይደለም። ምን እየተበላ ምንስ የቤት ኪራይ እየተከፈለ ነው ራስህን የምታዳምጠው? ‘ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ፣ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ?’ የተባለው ለእንደኛ ዓይነቱ ነው፤›› ሲለው ሳቁ ኑሮ ላይ የሚያላግጥ ለበጣ መሆኑ ገባን። ‹‹እኛ እንዲህ ሲገባን መንግሥት አልገባው ብሎ ነው ሹም እየጨመረ በጀት የሚጨርሰው?›› ብሎ አንዱ ቢናገር፣ ‹‹ኧረ ጨዋታው ወዲህ ነው፤›› አለው ወጣቱ። አንዳንድ ሰው ኳስን በመሬት አድርጎ የመጫወት ብልኃቱ ጠፍቶበታል እኮ? ‹‹ኳስ በአየር ድሮ ቀረ›› የሚል ተናጋሪ እስኪመጣ ድረስ እንጠብቅ ታዲያ?

ድንገት አንድ እጅ ክንዴን ነካ ሲያደርገኝ ዞርኩ። ከቆንጂት ጋር ሙግት ገጥሞ የነበረው ወጣት በዓይኑ እየጠቀሰ ‹‹ቦታ ትቀይረኝ?›› አለኝ ኮስተር ብሎ። ታክሲያችን ስትቆም ጠብቄ ቦታ ቀየርኩት። ‹‹ወይ ዘመን! አይ የእኛ አለመታደል?›› ይላሉ አዛውንቱ። ቆንጂትና ወጣቱ ወዲያው ሞቅ ያለ ጨዋታ ጀምረዋል። አዛውንቱ ወያላውን፣ ‹‹አንተ ቫት አታስከፍልም? ዝም ብለህ ታያለህ?›› ሲሉት በሳቅ ፈረስን። ‹‹ከምንበላው የሚቆረጥብን አይበቃምና ነው ደግሞ ከፍቅራችን ቫት የሚቆረጠው?›› ሲላቸው በዓይናቸው ጠቅሰው በእጃቸው ‹‹ብራቮ›› አሉት። እሱም አፀፋውን መለሰላቸው። አዛውንቱ ቀጥለው፣ ‹‹በመዋደድና በመፋቀር የታደለ ትውልድ ከቶ እንደዚህ የት አየን?›› አሉ ለራሳቸው

ብሔራዊ ውሸት?

ፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር

የባለአክሲዮኖች 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ

የስብሰባ ጥሪ

ለተከበራችሁ የፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር ባለአክሲዮኖች!

ፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማኅበር የባአክሲዮኖች 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ታህሳስ 13/2005 ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ሆቴል ስለሚያካሄድ ባለአክሲዮች በጠቅላላ ጉባኤው ላይ እንዲገኙ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡

የጉባኤው አጀንዳዎች

1. ረቂቅ አጀንዳ ማጽደቅ፣

2. የዳይሬክተሮች ቦርድን ሪፖርት መስማት፣

3. የውጭ ኦዲተሮችን ሪፖርት መስማት፣

4. በቀረቡት ሁለቱ ሪፖርቶች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማስተላለፍ፣

5. ለመጪው ዘመን የውጭ ኦዲተሮችን መምረጥና ክፍያቸውን መወሰን፣

6. በጎደለ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ምትክ መምረጥ፣

7. የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን ወርሃዊ አበል መወሰን፣

8. የጉባኤውን ቃለ ጉባኤ ማጽደቅ፡፡

ማሳሰቢያ፡-በጉባኤው ላይ ለመገኘት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች፣ ጉባኤው ከሚካሄድበት ቀን በፊት ሱማሌ ተራ አካባቢ በሚገኘው የኢንሹራንሱ ዋና መ/ቤት በመገኘት፣ የውክልና ፎርም በመሙላት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት የተሰጠ በስብሰባው ላይ ለመገኘትና ድምጽ ለመስጠት የሚያስችል ውክልና ዋናውን እና አንድ ፎቶ ኮፒ፣ እንዲሁም የመታወቂያውን ዋናና ፎቶ ኮፒ በጉባኤው እለት ይዞ በመቅረብ በጉባኤው መሳተፍ ይችላል፡፡

ፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር

የዳይሬክተሮች ቦርድወደ ገጽ 42 ዞሯል

Page 17: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 17 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ማስታወቂያእንረዳዳ ሁለገብ ኃ/የተ/ሸ/ማ በቦሌ ክ/ከ ወረዳ 03 ቦሌ 2ሺህ ሀበሻ የባህል ምግብ ቤት ጀርባ በማጠናቀቅ ላይ ባለው ዘመናዊ ሕንጻው ለመጋዘንና ለጂምናዚየም የተዘጋጁ ክፍሎችን ከበቂ መኪና ማቆሚያ ጋር በጨረታ አወዳድሮ ለማከራየት ይፈልጋል፡፡

ተጫራቾች በማንኛውም የሥራ ሰዓት በስልክ ቁጥር 0116-18-81-79 ወይም 0116-62-13-54 በመደወል ሕንጻውን መጎብኘትና የጨረታ ሰነድ በነጻ ወስደው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ጨረታውን በሰም በታሸገ ፓስታ ማህበሩ ጽ/ቤት ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታው ታህሳስ 17 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ በ4 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡ ማሕበሩ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡

ማስታወቂያ

የኦዲት ሥራ ማስታወቂያ ኢንተርሞን ኦክስፋም (ኦክስፋም ስፔን) የውጭ በጎ አድራጎት ድርጅት ሆኖ ህዳር 7 ቀን 2002 ዓ.ም በበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት አጀንሲ በምስክር ወረቀት ቁጥር 0736 ዳግም ተመዝግቦና ፈቃድ አግኝቶ የሚሰራ የልማትና የሰብአዊ ተራድኦ ድርጅት ነው፡፡

ድርጅታችን የ2012 በጀት ዓመት ሂሳብ ለማስመርመር (ኦዲት ለማስደረግ) ስለፈለገ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ የኦዲት ድርጅቶች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እአንገልጻለን፡፡

► ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ

► በሙያ ብቃትና በህጋዊነት ታውቀው በመንግስት መመዝገቡን የሚገልጽ

ማስረጃ ማቅረብ የምትችሉ

► የዘመኑን ግብር ከፍለው በ2004 በጀት ዓመት ፈቃዳቸውን ያሳደሱ

► የኦዲቲንግ በቂ የሥራ ልምድና ባለሙያ ያላቸው

► የታክስ መለያ ቁጥር (TIN NUMBER) ያላቸው

ተወዳዳሪዎች ለአገልግሎት የምታስከፍሉትን ዋጋ እና ሥራውን ሰርታችሁ የምታስረክቡበትን ጊዜ የሚገልጽ ሰነድ በማያያዝ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ከዚህ በታች በተጠቀሰው አድራሻ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

አድራሻ፡ ኢንተርሞን ኦክስፋም ደብረ ዘይት መንገድ ግሎባል ሆቴል አጠገብ ግሪክ ኤንባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው ጭላሎ ህንፃ 4ኛ ፎቅ

ስልክ ቁጥር +251 416 81 81 ፖ.ሳ.ቁ 933/1110

ኢ.ሜይል [email protected]

አዲስ አበባ

BIDS INVITATION FOR EXTERNAL AUDIT SERVICE

The Consortium of Self-help group Approach Promoters (CoSAP) is a non-profit-making and a non-governmental network of Ethiopian residents charity Organizations that are engaged in the promotion of the Self Help Group (SHG) program in the country. The consortium has been established in the line with FDRE Charities and Societies proclamation number 621/2009 with registration number 1590.CoSAP would like to appoint external auditors that can meet the following requirements for auditing accounts of the organization for the year ending December 31st 2012Submission requirements

Professional certificates and practicing certificate of the federal office of Auditor General & ACCA respectively.

Authorized auditors with grade C Renewed business license TIN Certificate Company Profile Clear presentation of price and date of commencement and submission of

the 2012 audit reportPLEASE NOTE

The date of submission of the 2012 audit report should not be latter than 6 of Feb 2013.

The audit will be based in Addis AbabaFurther information may be obtained up on requestAudit firms fulfilling the above requirements may submit their financial

and technical proposal up to Thursday, 20 December 2012 during office hour (Monday-Friday 8:00 am to 5:00 pm) to our office located around Africaunionsar-beth area behind national tobacco factory, love for children organization youth center building first floor.

Consortium of Self Help Group Approach Promoters (CoSAP)P.O.Box 26720/1000

Notice for Bid of Car RentJSI/L10K-ICCM Project would like to hire vehicles with driver for the year 2012 to carry out its field activities in Amhara , Oromia, Tigray and SNNPR regions. 1. Type of Vehicles:• 4WD with engine capacity of above (model 1994-2000 or 105) 4000CC with 5 seats and

above.2. Criteria:• The company should have renewed trade license for the year 2005 E.C. and should be VAT

registered. • Evidence with minimum experience of five years and recommendation letter, minimum

three vehicles registered under the company name, and evidence of availability of sufficient working capital to deploy as many vehicles as possible.

• The vehicles should have a commercial plate numbers (Code 3), comprehensive motor insurance coverage and valid annual technical inspection and

• The drivers should have a valid driving license. 3. Additional information:

•Closing date of the bid will be within 15 consecutive days after the date of this announcement. •A contract agreement shall be signed between the winning bidder and JSI/L10K-ICCM Project

Ethiopia,•Payment shall be effected every fifteen days after providing the required services,•JSI/L10K-ICCM Project reserves the right to reject all or part of this bid and to select service provider

viewed most suitable based on the selection criteria set by JSI.4. Required:

• Quotation of vehicle rental fees per day (with fuel, driver allowances and other related costs) for each type of vehicle according to its make, model and manufacture year. Also include terms in case of significant rise in fuel price.

Bidders who fulfill the stated criteria and conditions can submit their quotation and crednetials in a sealed envelope in one of the following address:

a. Mail to:Administration (Vehicle Rental Quotation),JSI/L10K-ICCM Project P.O.Box 13898,Addis Ababa

Orb. Hand deliver to JSI/L10K-ICCM Project Office, Winta Building, 1st Floor, Tel: 0116-620066

Page 18: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 18|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

VACANCY ANNOUNCEMENTYekatit Papar Converting Plc., a newly created private company formed by the merger of Yekatit Paper Converting Enterprise and Techno Printers which is engaged in paper converting, commercial printing and exercise book manufacturing invites qualified and competent applicants for the following vacant positions.

1-Production and technique Department ManagerMain tasks and responsibilities

• Planning, organizing, directing, coordinating and supervising the entire activities of the department.

• Ensures that the necessary manpower, equipment and facilities are effectively organized for success of the department’s goals.

• Sets production and performance targets along with defined KPIs based on the operational and strategic plans.

• Direct and control all workers under the department to ensure that they are properly motivated, trained and developed, and carry out their responsibilities

• Establishes planned and routine maintenance plan for machinery and equipments and asses machine to make projections of output capability.

• Directs scheduling of preventive as well as major maintenance programs required at different levels of workshops.

• Develops and recommends equipment management system for efficient operation, usage maintenance and replacement of equipments and machinery.

• Ensures that work orders are opened for each equipment and machinery to be required so that detailed information is available before and after repairs or maintenance are carried out.

Minimum Qualification

Bsc degree in Mechanical/ Industrial Engineering or related disciplines and 6 years of relevant work experience of which at least 3 years in management position in printing industry.

Place of work: Addis AbabaSalary and benefit packages: Attractive

2-Excutive secretary Main tasks and responsibilities•Prepare and manage Correspondences, appointments and reports•Handling incoming an outgoing letters•Create ,maintain and manage computer and paper filling systems•Perform special assignments as requested.

Educational Requirements•Degree or diploma in secretarial science and office management, Business

Administration or information technology from a recognized university or college.

•At least 2 and 4 year relevant work experience for degree and Diploma holders respectively

Skills•Effective verbal and communication skills•Stress and time management skills•Excellent computer skills

Place of work: Addis AbabaSalary: Negotiable

Applicants fulfilling the stated criteria could submit in person their application with CV and copy of testimonials within 10 consecutive days from the date of this announcement to the Human resource Department

Address: Yekatit paper converting PLC

The human resource department, 1st floorOpposite to Gerji – Mebrathail

Tel-+251-8-959035Mobile-+251-1-911526812

የጨረታ ማስታወቂያ አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም አ.ማ. ለተቋሙ አገልግሎት የሚውል

• የቁጠባ ደብተር

• የቼክ መክፈያ ቫውቸር በጨረታ አወዳድሮ ለማሳተም ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በጨረታ ሰነዱ ላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች ማሟላት የምትችሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

በዚህም መሰረት፣ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፣

• የዘመኑን ግብር የከፈሉና የታደሰ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ እንዲሁም የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባቸዋል፣

• የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ለጨረታው የተዘጋጀውን ሰነድ መግዛት ይቻላል፣

• ማንኛውም ተጫራች ላቀረበው ዋጋ ማስከበሪያ የሚሆን ጠቅላላ ዋጋ 2% የጨረታ ማስከበሪያ በCPO ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርበታል፣

• በጨረታው ለተሸነፉ ተወዳዳሪዎች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ አሸናፊው ከታወቀ በኋላ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፣

• ማንኛውም ተጫራች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ቢሮ ቁጥር 15 በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚችል ሲሆን ጨረታውም በቀጣዩ የሥራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 19 ውስጥ ይከፈታል፣

• ማንኛውም ተጫራች የህትመት ሰነዶችን ናሙና በመመልከት ዋጋ ማስገባት ይኖርበታል፣

• ተቋሙ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፣

• ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 0911648461/0913006774 መጠየቅ ይቻላል፡፡

አድራሻ፡- አቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ፊት ለፊት፣

አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም አ.ማ.

VACANCY ANNOUNCEMENT

Keangnam Enterprises Ltd., a South Korean Construction Company, would like to invite applicants for the following position:

No Job Title Quantity Qulification Work Experience

1 Procurement Manager

1 BA, Degree in Supply & Management

3 years & above (Construction

Company) 2 Senior

Material Engineer

1 BSC in Civil Engineering

10 years & above (Road Construction)

Place of work : Jimma-Bonga Road Upgrading Project

( Contract-1)

Salary : Negotiable

Terms of Employment: On contract basis

Interested applicants who fulfill the above requirements can send non-returnable application, CV and copies of relevant documents within 7 days from the date of this announcement to the following address: Keangnam Enterprises Ltd.

Ethiopia Branch Office Administration Department

P.O.Box 2351 Addis Ababa

Or E-mail to [email protected]

Page 19: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 19 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ል ና ገ ር

በእያሱ ማንከልክሎት

ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓ.ም. አዲሱ ገበያ አካባቢ የሚገኘው የምርጫ ጣቢያ ለመምረጥ የደረስነው ገና ጎህ ሲቀድ ቢሆንም፣ ከእኛ በፊት የደረሱ መራጮች የፈጠሩት ሠልፍ በጣም ረጅም ነበር:: የዚያ ሠልፍ ርዝመት በግምት ከ500 ሜትር በላይ ይሆን ነበር ብል ፈጽሞ የተጋነነ አልነበረም:: ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ እኔና ወንድሜ ድምፃችንን ሰጥተን ከምርጫ ጣቢያው ስንወጣ፣ አንዲት በዕድሜ የከበሩ እናት፣ ‹‹አምላኬ ሆይ ይህንን ምርጫ የሰላም አድርገው፤›› እያሉ ፈጣሪያቸውን ሲማፀኑ ሰማናቸው:: የእሳቸው ብቻ ሳይሆን የብዙኅኑ ሕዝብ ምልጃም ነበር:: በዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ሳይቀር በሰላም መጠናቀቁ የተነገረለት ያ የምርጫ ቀን ምን ተከትሎት እንደመጣ ለምናስታውስ ዛሬም ድረስ ያንገበግባል::

ምርጫ 97 በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ምዕራፍ ሊከፍት የሚችል መልካም አጋጣሚዎችን ይዞ ቢመጣም፣ እንዳይሆኑ ሆኖ ለበርካታ ወገኖች መሞት፣ መታሰር፣ መሰደድና ዛሬም ድረስ ለዘለቀ ቁርሾ ምክንያት ሆኗል:: ከዚያ ወዲህ ‹‹ምርጫ›› የሚለው ቃል ለብዙዎች አስደንባሪ፣ አስፈሪና ከጀርባው ደስ የማይል መንፈስ የያዘ እየመሰለ ነው:: በምርጫ 2002 ወቅት በምርጫው ዋዜማ ቀናት በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የታየው ጭርታ የ97 ምርጫ የዞረ ድምር ፍራቻ እንደነበር ማንም አይስተውም:: በምርጫ 2002 ኢሕአዴግ በዚያን ያህል መጠን ምርጫውን አሸነፈ መባሉ ይህንን ሁሉ እውነታ ጥርት አድርጎ ያሳያል:: የተሽመደመዱ ተቃዋሚዎች ውር ውር ባሉበት በእዚያ ምርጫ ኢሕአዴግ ተራራ አክሎ ማሸነፉ የሚገርም አልነበረም::

አሁን ደግሞ የአካባቢ ምርጫ ለማካሄድ ለመጪው ሚያዝያ ወር ቀጠሮ ተይዟል:: በተለይ በአዲስ አበባ የሚካሄደው ምርጫ ለመጪው ብሔራዊ ምርጫ እንደ መንደርደሪያ ያገለግላል ተብሎ በሚጠበቅበት በዚህ ወቅት ምርጫ ቦርድና ተቃዋሚ ፓርቲዎች የጀመሩት እንካ ሰላንቲያ መሰማት ጀምሯል:: ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ምርጫ የሚናፍቀው የአገራችን ሕዝብ ምርጫ በመጣ ቁጥር ለምን ይሳቀቃል? ምርጫን ሁሉን አቀፍ ሆኖ ደረጃውን በጠበቀ የምርጫ ሕግ መሠረት መከናወን ሲኖርበት ለምን የውዝግብ መነሻ ይሆናል? አንድ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ቁርጠኝነት ያለው አገር ምርጫን የሕዝብ ፍላጎት መግለጫ ሲያደርገው እኛ ዘንድ ግን ሕዝብ ለምን አይከበርም? ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ሐሳቦች በነፃነት የሚንሸራሸሩበትና የነፃነት ተምሳሌት መሆኑ እየታወቀ ከዚያ ተቃራኒ ወደሆነ አቅጣጫ መጓዝ ለማን ይበጃል? በርካታ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል::

ብዙ ጊዜ ስለ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሲነሳ የሚነሱ ዋነኛ ቁም ነገሮች አሉ:: ለምሳሌ አንዱ የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ነው:: ሌላው ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ነው:: በእነኚህ መብቶች ላይ ተመሥርቶ የሚመጣው ምርጫ ነው:: ሰብዓዊ መብቱ የሚከበርለት ዜጋ በነፃነት የፈለገውን አመለካከትና አቋም የመያዝ መብት አለው:: ይህ መብት የተከበረለት ዜጋ የፈለገውን በገዛ ፈቃዱ የመምረጥ መብት ይኖረዋል:: ይህ ሁሉ ግን በሚፈለገው መንገድ ይጓዝ ዘንድ የተመቻቸ ሜዳ አለ ወይ? የሚለውን ጥያቄ ያስነሳል:: ለዚህስ ፍላጎትና ቁርጠኛ ዓላማ አለ ወይ? የሚል ተከታይ ጥያቄም ያስነሳል::

ኢትዮጵያ ውስጥ ስለ መድብለ ፓርቲ ሥርዓት መነገር ከጀመረ ሁለት አሥርት አልፈዋል:: በዚህ ጊዜ ውስጥ አራት ብሔራዊ ምርጫዎች ቢካሄዱም ምርጫዎቹ ሁሌም በውዝግብ ነው የሚቋጩት:: በምርጫ ዋዜማ፣ በምርጫ ዕለትና በድኅረ ምርጫ የሚሰሙ ሽኩቻዎችና ትንቅንቆች እንኳን ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት አይደለም ለተራ ጉዳይ እንኳ የሚመጥኑ አይደሉም:: ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግና ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዕጩዎች ምዝገባ፣ በምርጫ ክርክርና በድምፅ ቆጠራ ወቅቶች የሚያነሱዋቸው ውዝግቦች በኢትዮጵያ ውስጥ ምርጫ መልኩን እንዲቀይር እያደረጉት ነው:: በምርጫ 97 እስከ ውጤት መገለጽ ጊዜ ድረስ ያየነው ዓይነት መልካም ድባብ ተበላሽቶ ምርጫ እያስጠላ ነው:: ይህ ዓይነቱ ችግር ሁሌም ለምን የተለመደ ሆነ ብለን ስንጠይቅ ለመወያያ የሚሆኑ ጉዳዮችን ማንሳት እንችላለን::

በመጀመርያ የአገሪቱ የፖለቲካ ሥነ ምኅዳር የሚባለው የመጫወቻ ሜዳ ጉዳይ መነሳት አለበት:: ኢትዮጵያ ውስጥ ገዥው ፓርቲና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ሁሌም ከማያግባባቸው መካከል ስንጀምር የመጀመርያው የመንግሥት መገናኛ ብዙኅን አጠቃቀም ጉዳይ ጎልቶ ይወጣል:: የመንግሥት የመገናኛ ብዙኅን አገልግሎታቸው ሁሉንም ዜጎች በእኩልነት ማዳረስ ሲገባው በሚገርም ሁኔታ የገዥው ፓርቲ ልሳን ናቸው:: ገዥው ፓርቲ እንደማንኛውም ፓርቲ የራሱ ልሳን ኖሮት ዓላማውን በእዚያ በኩል ማስረዳት ሲገባው፣ የመንግሥት የመገናኛ ብዙኅን ቀንና ሌሊት ይህንን ሲያስፈጽሙ ይታያሉ:: በሌላ በኩል ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመንግሥት መገናኛ ብዙኅን የሚያገኙት ሽፋን እጅግ በጣም አነስተኛ ከመሆኑም በላይ፣ ያችን ትንሽ ሽፋን እንኳ በአግባቡ አያገኙም:: በዚህ ዓይነቱ አሠራር ምክንያት የመጫወቻው ሜዳ እጅግ በጣም ጠቧል:: የመገናኛ ብዙኅኑ ተደራሽነት ውስን በሆነባት አገር ውስጥ ምርጫው በዲሞክራሲያዊ መንገድ እየተካሄደ ነው ሲባል ደስ አይልም::

የፖለቲካ ፓርቲዎች ሥልጣን ሲይዙ በተወሰነ ደረጃ የተሻለ ተጠቃሚነት እንዳላቸው

በዓለም አቀፍ ደረጃም የታወቀ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን አስተዛዛቢ ነው:: ለምሳሌ በተለያዩ ጊዜያት ወደ ኢትዮጵያ ተጋብዘው ከመጡ ዓለም አቀፍ የምርጫ ታዛቢዎች መካከል ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው የአውሮፓ የምርጫ ታዛቢዎች ልዑክ ያወጣቸውን ሪፖርቶች ስናገላብጥ የምናገኘው ይኼንኑ ነው:: የአውሮፓ ምርጫ ታዛቢዎች ሪፖርት ውስጥ በመንግሥትና በገዥው ፓርቲ መካከል ያለውን ልዩነት ለማወቅ ያዳግታል የሚል አስተያየት ተጽፎ ይገኛል:: ምንም እንኳ መንግሥት ይህንን በተደጋጋሚ ቢያስተባብልም እኛ ዜጎች ራሳችን በተግባር የምናውቀው ነው:: የመንግሥት ቢሮዎች፣ የወረዳና የቀበሌ መስተዳድሮች፣ የመንግሥት ተሽከርካሪዎች፣ ሠራተኞች፣ ወዘተ ከተሰጣቸው መንግሥታዊ ሥራ ውጪ ለምርጫ ቅስቀሳና ማስፈጸሚያ ሲውሉ ይታያሉ:: ይህ በራሱ ፍትሐዊ ምርጫ እንዳይኖር ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል::

በምርጫ ቦርድ አሰያየም ላይም የሚሰማው እሮሮ ለረጂም ጊዜ የምንሰማው ነው:: ምርጫ የሚያስፈጽሙ ወገኖች የገዥው ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ናቸው የሚል ክስ በተደጋጋሚ በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንሰማለን:: የምርጫ ቦርድን ገለልተኝነት በተግባር የሚያሳየን ስለማይኖር ወይም ቦርዱ ራሱ ገለልተኛ ለመሆኑ ተጨባጭ ማረጋገጫ ስለማይሰጥ ምርጫን ፍትሐዊ ብሎ ለመቀበል ይቸግራል:: ወደተለያዩ ክልሎች ስትሄዱ ምርጫ አስፈጻሚ የነበሩ ግለሰቦች የፖለቲካ ካድሬ ሆነው ታገኛላችሁ:: ቦርዱ በተለያዩ ጊዜያት በእንዲሀ ዓይነት ግለሰባች ላይ የማግለል ወይም የማባረር ዕርምጃ እወስዳለሁ ቢልም እሮሮው አሁንም ይሰማል:: በአጠቃላይ የብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ገለልተኝነት ጉዳይ አሁንም በትልቁ ጥያቄ የሚነሳበት ነው:: ምርጫን የሚያስፈጽም አካል ገለልተኝነት ጥያቄ ውስጥ ወድቆ ምርጫ ፍትሐዊነቱ እንዴት ይገለጻል?

ገዥው ፓርቲ በሀብት፣ በአባላት፣

በደጋፊዎችና በተለያዩ ጉዳዮች እየፈረጠመ ሲሄድ በተቃራኒው ግን ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች እየኮሰመኑ ናቸው:: ገዥው ፓርቲ አንድ ለአምስት በሚል ከከተማ እስከ ገጠር ደጋፊዎችን እያቧደነ ሲያስተባብር ተቃዋሚዎች ምን ያህል አባላት እንዳሉዋቸው እንኳን አይታወቅም:: ገዥው ፓርቲ ነጋዴዎችና ባለሀብቶች ደጋፊ ፎረም አቋቁመውለት ሚሊዮኖችን ሲረጩለት ተቃዋሚዎችን ዞር ብሎ እንኳ የሚያያቸው የለም:: እዚህ ላይ ገዥው ፓርቲ ለምን እንዲህ አደረገ ወይም ተደረገለት እያልኩ አይደለም:: ይህ መደረጉ ምንም ክፋት የለውም:: ችግሩ ግን ተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላትን ለማፍራት፣ ደጋፊዎችን ለማግኘት፣ የማቴርያልና የቴክኒክ እገዛ ሲያፈላልጉ መሰናክል አያጋጥማቸውም ወይ? የሚለው ሁሌም የማብሰለስለው ነው:: ገዥው ፓርቲ ለራሱ የሚደረግለት ለሌሎች እንዲደረግ ቀና ልቦና የለውም:: ቢኖረው ኖሮማ ሌላው ቀርቶ የሆቴልና የተቋማትን አዳራሽ ለማግኘት ተቃዋሚ ፓርቲዎች መከራቸውን አያዩም ነበር:: እንዲህ ዓይነቱ ችግር ደግሞ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ጠንቅ ነው::

የፖለቲካ ሥነ ምኅዳር መጣበብ ችግር

የሚመነጨው ከገዥው ፓርቲ በኩል ብቻ ነው ብሎ መደምደም ኢፍትሐዊነት ነው:: ባለፉት 21 ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠሩ ፓርቲዎች ከዚህ አንፃር የነበራቸው አስተዋጽኦ ምን ይመስላል በማለት ጥያቄ ማቅረብ ግድ ይላል:: በአገሪቱ ውስጥ ስልሳ ያህል የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳሉ እንሰማለን:: ነገር ግን ብዙ ጊዜ በምርጫ ሰሞንና በአንዳንድ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ብቅ የሚሉትን ፓርቲዎች ስናይ የምናነሳቸው ጥያቄዎች አሉ:: ለምሳሌ ኢዴፓ፣ መኢአድ፣ መድረክና የመሳሰሉት ፓርቲዎች አሉ:: በቅርቡ ሰላሳ ምናምን ፓርቲዎች የተጣመሩበት ስብስብ መኖሩንም ሰምተናል:: እነዚህ ፓርቲዎች ተዋህደው መንቀሳቀስ ሲገባቸው በተናጠል ይታያሉ:: የሁሉንም ፕሮግራምና ማኒፌስቶ ስታዩ ይህን ነው የሚባል ልዩነት የላቸውም:: ልዩነት ቢኖራቸው እንኳ አስታርቀው መጓዝ ሲገባቸው ጊዜያቸውን፣ ሀብታቸውን፣ የሰው ኃይላቸውንና ጥንካሬያቸውን ሲበታትኑ ይታያሉ:: ከዚያ አልፎ ተርፎም እርስ በርስ ይናቆራሉ:: ተበታትነውና ተለያይተው ለምርጫ ሲቀርቡ የሕዝቡን ድምፅ ይከፋፍሉና ለሽንፈት ይዳረጋሉ:: ከዚህ በተጨማሪም በብዛት ድምፃቸው የሚሰማው ምርጫ ሲደርስ ብቻ ነው:: ከዚያ ውጪ ውሎአቸው አይታወቅም::

ከተወሰኑት በስተቀር ብዙዎቹ የዲሞክራሲ ፅንሰ ሐሳብ የገባቸው አይመስሉም:: የተለያዩ አመለካከቶችን ማስተናገድ ስለማይፈልጉ ሲተቹ ይቆጣሉ:: በውስጣቸው የዲሞክራሲ አስተሳሰብ ዘልቆ ባለመግባቱ ከድጋፍ በስተቀር ትችት አይፈልጉም:: ብዙዎቹ ከገዥው ፓርቲ የተሻለ መሆናቸውን ሕዝብን የሚያሳምኑበት አማራጭ ሐሳብ የላቸውም:: አለን ቢሉ እንኳ ሕዝቡ ዘንድ መድረስ አልቻሉም:: የገዥው ፓርቲ ጫና ከሚያደርስባቸው በላይ የውስጥ ችግሮቻቸው ይብሳሉ:: ትግል ውስጥ መግባታቸውን የረሱ ይመስል በትንሽ በትልቁ ችግር ሲላቀሱ ማየት የተለመደ ነው:: የብዙዎቹ ፓርቲዎች የገንዘብ አቅም የተመናመነ ነው:: በቅጡ መዝግበው

የያዙዋቸው አባላት ስለመኖራቸው እንኳን ያጠራጥራል:: የገዥውን ፓርቲ እንቅስቃሴ እየተከታተሉ የጉሸማ እንቅስቃሴ ከማድረግ ውጪ የፖሊሲ ጥያቄዎችን እያነሱ ሲሞግቱ አይታዩም:: ለምሳሌ ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁለት ተጨማሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ለምን ሾሙ ብለው ቡራ ከረዩ ማለታቸው የዚህ ማሳያ ነው:: ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ብቻ እንደተሾሙ፣ የተቀሩት ሁለቱ ግን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ (Portfolio) ሥራ ለማቀላጠፍ እንደመጡ ቢያስረዱም ወደ ፍርድ ቤት እንሄዳለን የማለታቸውን ዜና አንበበናል:: እንዲህ ዓይነት ውኃ የማይቋጥር አጀንዳ ይዘው የሚካለቡ ተቃዋሚዎች ለዲሞክራሲያችን መቀጨጭ ምክንያት ቢሆኑ ምን ይገርማል? የሚያሳዝነው ደግሞ የኢሕአዴግን ዱካ ብቻ እየተከተሉ ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ተቃዋሚዎች መቼ ይሆን ወደ ፓርቲ ፖለቲካ ሥራ የሚገቡት?

ብዙ ጊዜ ተቃዋሚዎች ‹‹የአዛውንቶች ክበብ›› ሆነዋል ሲባል እንሰማለን:: ‹‹መተካካት›› የሚለውን የኢሕአዴግ መርህ ለጊዜው እንተወውና የተቃዋሚው ጎራ ለውጥ አይፈልግም ወይ የሚል ጥያቄ ይነሳል:: ሁሌም በየነ ጴጥሮስ፣ መረራ ጉዲና፣ ኃይሉ ሻውል፣ ነጋሶ ጊዳዳ፣ ወዘተ የፓርቲ አለቆች ሆነው ሲታዩ ይህ ጥያቄ ቢነሳ አይገርምም:: ያለንበት ዘመን በከፍተኛ ደረጃ ለውጥ እየተካሄደበት ነው:: በፓርቲም ሆነ በአገር ደረጃ አንድ ሰው ከስምንት ዓመት በላይ ሥልጣን ላይ መቆየት እንደሌለበት ባልተጻፈ ሕግም ቢሆን ዓለም እየተስማማ ነው:: ለሁለት አሥርት ያህል አንድ ፓርቲ ታቅፈው የተቀመጡ ሰዎች በኃይል እስኪወገዱ ድረስ የሚነቃነቁ አይመስሉም:: ብዙዎቹ ከዘመኑ አስተሳሰብ ጋር የሚራመድ አጀንዳ ሲያቀነቅኑ አይታዩም:: ሁሌም ከውግዘትና ከማሳጣት ያላለፈ ግልብ ፖለቲካ ያራምዳሉ:: ውጤቱ ደግሞ ሁሌም ዜሮ ነው:: ወጣቶችን የማይስብ የፖለቲካ ፓርቲና አጀንዳ ለአገሪቱ የፖለቲካ ሥነ ምኅዳር ራሱን የቻለ ፈተና ነው::

በእንዲህ ዓይነቱ ድባብ ውስጥ የሚካሄድ ምርጫ ውጤቱ ቀድሞ የሚተነበይ ሲሆን፣ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ምንም ፋይዳ የለውም:: ሁሉን አቀፍና አሳታፊ የሆነ የፖለቲካ ሥርዓት በሌለበት አገር ውስጥ ምርጫን ‹‹ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ፣ እንከን የለሽ፣ ወዘተ›› እያሉ ማውራት ያስተዛዝባል:: መደላድሉ ባልተመቻቸበት ሁኔታ ውስጥ ምርጫው ሲደርስ አላስፈላጊ ትንቅንቅ እየተካሄደ በሰው ልጆች ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ይደርሳል:: ምርጫ የሕዝብ ይሁንታ የሚገለጽበት ትልቅ ሥርዓት መሆን ሲገባው የጉልበተኞችና የእልኸኞች መታገያ መድረክ ይሆናል:: የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መገለጫ የሆኑት ሰብዓዊ መብትና ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እየተጨፈለቁ መቀጠል ስለሌለባቸው ለአገር ህልውና ሲባል አንድ መላ ሊመታ ይገባል እላለሁ::

እኔ እንደ መፍትሔ የማቀርበው በመጀመርያ ደረጃ የአገራችን ፖለቲከኞች ላለፉት 40 ዓመታት ይዘውት የመጡትን የጥላቻ ፖለቲካ ማስወገድ አለባቸው:: በጥላቻና በሴራ የተተበተበው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ራሱን ለዲሞክራሲያዊ አስተሳሰቦች ማስገዛት አለበት:: ውይይትና ድርድር ከጠብና ካላስፈላጊ ድርጊቶች የሚታደጉ የዲሞክራሲ ሥርዓት መሣርያዎች በመሆናቸው ፖለቲከኞች ለድርድር ልባቸውን መክፈት ይኖርባቸዋል:: በአምባገነናዊ አስተሳሰብ የታወሩ የሥልጣን ጥመኞች ሕዝብን ያክብሩ:: የሥልጣን ምንጭ ነው እስከተባለ ድረስ የሕዝብ ድምፅ ይከበር:: ሰብዓዊ መብቶች ይከበሩ:: ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ ሕገ መንግሥታዊ መብት በተግባር ይዋል:: የሕግ የበላይነት በተግባር ይረጋገጥ:: ከሙስና፣ ከአድሎዎና ከራስ ወዳድነት የፀዳ ሥርዓት እንዲፈጠር ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ኃላፊነት የተሞላበት አሠራር ይኑር:: ይህ መንግሥትን የሚመራው ፓርቲ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላትና የመላው ዜጎች ኃላፊነት መሆን አለበት:: አለበለዚያ ምርጫ በመጣ ቁጥር የሚናጠው ሕዝባችን ከምሬት በቀር ጠብ የሚልለት ነገር አይኖርም:: ምርጫን ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መጠቀም ሲገባን እየተናቆርንበት መቀጠል የለብንም::

ምርጫ በመጣ ቁጥር ለምን እንሳቀቃለን?

ምርጫ 97 በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ምዕራፍ ሊከፍት የሚችል መልካም አጋጣሚዎችን ይዞ

ቢመጣም፣ እንዳይሆኑ ሆኖ ለበርካታ ወገኖች መሞት፣ መታሰር፣ መሰደድና ዛሬም ድረስ ለዘለቀ ቁርሾ

ምክንያት ሆኗል:: ከዚያ ወዲህ ‹‹ምርጫ›› የሚለው ቃል ለብዙዎች አስደንባሪ፣ አስፈሪና ከጀርባው ደስ የማይል መንፈስ የያዘ እየመሰለ ነው:: በምርጫ

2002 ወቅት በምርጫው ዋዜማ ቀናት በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የታየው ጭርታ የ97 ምርጫ የዞረ

ድምር ፍራቻ እንደነበር ማንም አይስተውም::

Page 20: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 20|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

Vacancy announcementFederal Ministry of Health

Federal Ministry of Health and the regional bureau of Health would like to recruit the Following Consultants for Tuberculosis Prevention and Control Program through the Global Fund Round ten Grant.

Terms of reference for National TB, Leprosy and TB/HIV Control Consultant

Background

Tuberculosis, Leprosy and HIV/AIDS are among the leading infectious diseases in Ethiopia results physical, psychosocial and emotional sufferings and jeopardizes the lives of hundred thousands of people each year.

In the era of HIV/AIDS and poverty Tuberculosis is alarmingly increasing. According to the WHO estimate for Ethiopia, there are 261 all forms of TB cases per 100,000 populations. Hence prompt identification and treatment of these infectious cases is the ultimate gateway for the control of the disease. National Tuberculosis prevention and control program should achieve and maintain at least 70% of case detection rate and 85% of treatment success rate to contain the spread of the infection in the population and prevent emergence and spread of Multi Drug Resistant (MDR) Mycobacterium Tuberculoses strain.

Cognizant of the burden and its impact on socioeconomic development, Ethiopia has embarked on Millennium Anti-TB campaign with the main programmatic and logistics support from the Global fund grants to fight HIV/AIDS, Tuberculosis and Malaria (GFATM) and the National Tuberculosis control program has been benefiting from this grant since 2003. The round 10 proposal for Tuberculosis control is approved by the Global fund Secretariat and grant agreement was signed on 22th of March 2012 to implement the proposed activities. In order to ensure successful implementation of the program (TBL and TB-HIV)and maximum utilization of the support from GF the Federal Ministry of Health would like to Federal Ministry of Health and the regional bureau of Health would like to recruit Consultants for Tuberculosis Prevention and Control Program through the Global Fund Round ten Grant.

2. Terms of reference for the consultant• Provide technical support in all aspects of TB, Leprosy and TB/HIV control

to respective National TB program, Regional Health Bureaus, Zonal Health Departments, Woreda Health Offices and Health Facilities to achieve the planned targets.

• Provide support on capacity building at National, Regional, Zonal, Woreda and Health Facility levels.

• Coordinate and involve in Monitoring and Evaluation activities of the TB, Leprosy and TB/HIV collaborative activities.

• Brief regularly the FMoH the status of the program implementation, stock management and financial utilization.

• Assist the Coordination and supervision of the implementation of GF supported activities, financial utilization and liquidation, logistics management and monitoring and evaluation in the region.

• Compile, prepare and submit complete, timely and accurate TB, Leprosy, and TB/HIV monthly, quarterly, biannually and annually reports to the RBH & FMoH (TLCT) on program implementation, Logistics (Drug and Laboratory Supplies, financial utilization), EQA and other practices important for the successful implementation of Tuberculosis, Leprosy and TB/HIV prevention and control program.

• Strengthen Data management system of regional TBL and TB/HIV collaborative activities.

• Respond timely to the National Tuberculosis and Leprosy control program and/or focal person FMOH on any query and required information of the TBL and TB/HIV collaborative activities.

• Develop different reports, consulting documents and communicate to concerned officials at the ministry and partner organizations

• Facilitate administrative and financial utilization, collection and distribution of TB, Leprosy and TB/HIV supplies in connection with the implementation of the planned activities.

• Supervise and give timely feedback to regional Health bureau on the prevention, diagnosis and treatment activities of TB, Leprosy and TB/HIV.

• Develop tools and participate in the Integrated Supportive Supervision to the regional health bureaus, health facilities and other sub recipients and develop

reports and communicate the findings to the state minister, the department and other concerned bodies.

• Coordinate and organize advocacy, communication and social mobilization activities on TB, Leprosy and TB-HIV.

• Participate in planning, monitoring and evaluation of TB, Leprosy and TB/HIV activities/meetings.

• Conduct other duties given by the National TB focal person, Agrarian Health Promotion and Disease Prevention directorate and higher officials in the ministry.

3. Position= National TB, Leprosy and TB/HIV Control Consultant

3.1 Duty Station:- Federal Ministry of Health Agrarian Health Promotion and Disease Prevention Directorate , Addis Ababa

3.2 Number consultant =1

3.3 Qualification MD + MPH or ,BSC in Nursing + MPH or, BSc in Health Officer + MPH

3.4.Work Experience: 4 Years and above experience in public health and Program management with special focus in TBL, TB/HIV program

3.5. Salary= Negotiable.

3.6 Term of employment: One year contract with possible extension based on the merit and Performance of the incumbent.

Interested applicants are invited to submit their non returnable applications, CVs and copies of all documents together with their original document within (10) days from the first announcement to:

FEDERAL MINISTRY OF HEALTHHUMAN RESOURCE DEVELOPMENT AND ADMI.

DIRECTORATEP.O.BOX: 1234

TEL: 0115-515425ADDIS ABEBA ETHIOPIA

Vacancy announcementFederal Ministry of Health

Terms of Reference for GF National Consultant for PPM DOTS1. Background:

Tuberculosis, Leprosy and HIV/AIDS are among the leading infectious diseases in Ethiopia results physical, psychosocial and emotional sufferings and jeopardizes the lives of hundred thousands of people each year.

In the era of HIV/AIDS and poverty Tuberculosis is alarmingly increasing. According to the WHO estimate for Ethiopia, there are 261 all forms of TB cases per 100,000 populations. Hence prompt identification and treatment of these infectious cases is the ultimate gateway for the control of the disease. National Tuberculosis prevention and control program should achieve and maintain at least 70% of case detection rate and 85% of treatment success rate to contain the spread of the infection in the population and prevent emergence and spread of Multi Drug Resistant (MDR) Mycobacterium Tuberculoses strain.

Cognizant of the burden and its impact on socioeconomic development, Ethiopia has embarked on Millennium Anti-TB campaign with the main programmatic and logistics support from the Global fund grants to fight HIV/AIDS, Tuberculosis and Malaria (GFATM) and the National Tuberculosis control program has been benefiting from this grant since 2003. The round 10 proposal for Tuberculosis control is approved by the Global fund Secretariat and grant agreement was signed on 22th of March 2012 to implement the proposed activities. In order to ensure successful implementation of the program (TBL and TB-HIV)and maximum utilization of the support from GF the Federal Ministry of Health would like to employ Regional Tuberculosis, Leprosy and TB-HIV prevention and control officers on contractual basis to support and intensify the program implementation and monitoring at grass root level.

The Federal Ministry of health of Ethiopia is developing various strategies to accelerate DOTS expansion and reach as many TB cases as possible. One of the key strategies currently being implemented is Private Public Mix (PPM) DOTS initiative: Given the need for rapid expansion of DOTS and the objective of enhancing early case detection in Ethiopia, involvement of the private sector in TB prevention and control is a necessity included in the National Strategic Plan,

ማስታወቂያ

Page 21: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 21 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

and recommended by major International Organizations. The rationale behind this increasing partnership is expressed among other things by the fact that a significant proportion of TB cases go to private facilities as a first point of contact. The Private-Public Partnership (PPM) is likely to facilitate awareness on the disease, early case detection, proper case holding, TB-HIV collaborative activities and recording and reporting. For the scaling up of the implementation of PPM DOTS across the country, the Ministry is hiring a national PPM DOTS Consultant.

2. Terms of reference for the consultant• Coordinate and report to TB team on all activities related to the collaboration

with the private sector (NGOs and private facilities) with regard to TB and TB/HIV control, and create successful partnership among partners and stakeholder.

• Plan, support and monitor a phased scaling up of TB/HIV collaborative activities in the private sector in order to meet the national planned targets.

• Establish regular and documented communication and linkage with the Regional health Bureaus for the assessment, the selection and follow up of private facilities to be involved in PPM DOTS implementation

• Update PPM DOTS Implementation Guideline according to the needs identified (users remarks, changes in regimen etc)

• Provide typing and clear mapping of the various contributions from the private facilities in the implementation of PPM DOTS (i) ACSM and stigma reduction, (ii) participation to diagnosis with/without initial treatment phase, (iii) comprehensive DOTS care and (iv) TB and HIV collaborative activities.

• Collaborate closely with the TB Team data manager and regional TBL and TBL/TBHIV program officers and coordinators to extract PPM monitoring and evaluation data, in particular the activities/contributions of the private sectors (not-for-profit and for-profit) to TB and TB HIV control activities and assist timely collection and processing of TB and TB/HIV quarterly reports from PPM DOTS implementing sites.

• Provide regular informative comparative feed back on TB and TB/HIV data and outcome for all PPM DOTS implementing facilities.

• Identify skill gaps and training needs on PPM DOTS (both among private implementers and public managers) and participate accordingly in training activities at various levels, particularly with the support of GF grant: in that respect he/she should organize and coordinate trainings for private sector health workers on the principles and implementation of PPM DOTS.

• Work closely with the ACSM consultant in developing and testing adequate specific advocacy materials and organizing advocacy forums on PPM DOTS .

• Closely follow up and facilitate the regular provision of manuals, reporting formats, supplies and logistics (reagent for laboratories, first line TB drugs) to implementing private health facilities.

• Carry out supportive and documented supervisions on existing PPM/TB implementing facilities, with clear focus on quality of care and on-site training. Principally, he/she should carefully monitor the proper utilization of TB drugs and the compliance with NTP recommendation for TB and MDR TB.

• Collect and report on all relevant experiences from various private facilities implementing PPM DOTS in order to disseminate selected “success stories”.

• Submit relevant proposals and participate in the execution of operational studies regarding PPM DOTS.

• Work with other stakeholders that are currently assisting the implementation of the Public Partnership (PPP) and PPM DOTS in particular.

• Conduct other duties given by the National TB focal person, Agrarian Health Promotion and Disease Prevention directorate and higher officials in the ministry.

3. Position= National Consultant for PPM DOTS3.1 Duty Station:- Federal Ministry of Health Agrarian Health Promotion and Disease Prevention Directorate , Addis Ababa

3.2 Number consultant =1

3.3 Qualification MD + MPH or ,BSC in Nursing + MPH or, BSc in Health Officer + MPH

3.4.Work Experience: 4 Years and above experience in public health and Program management with special focus in TBL, TB/HIV program

3.5.Salary= Negotiable.

3.6 Term of employment: One year contract with possible extension based on the merit and Performance of the incumbent.

Interested applicants are invited to submit their non returnable applications, CVs and copies of all documents together with their original document within (10) days from the first announcement to:

FEDERAL MINISTRY OF HEALTHHUMAN RESOURCE DEVELOPMENT AND ADMI.

DIRECTORATEP.O.BOX: 1234

TEL: 0115-515425ADDIS ABEBA ETHIOPIA

Jupiter TradingVacancy Announcement

Jupiter Trading, which is a company that distributes office equipments along with their maintenance, has been a leading company for the past 17 years in its sector. It stands out within the country with its cutting edge state-of –the-art technology introduction to Ethiopia.It has three branches within Addis Ababa, One in Nazreth-Adama, One in Hawassa, and one in Diredawa which are all equipped with best services.Jupiter Trading would like to invite competitive applicants in the following position/titles.1. Position/Title: ReceptionistReports to: Floor Manager/ Executive Secretary Required number: 1Required educational background: at least Diploma in Receptionist/Front Office OperationExperience: At least 1 year.Salary: As per the salary scale of the company.

Duties may include, but are not limited to the following.- Receives and screens visitors and telephone calls, takes messages,

schedules appointments for professionals (s) and/or management staff taking due and attention as to the timely dissemination of information to the appropriate body;

- Provides information to callers requiring knowledge of the company’s operations,

- Prepares and issues proforma a for potential customers;- Sorts, opens, and distributes incoming mail to staff: associates incoming

correspondence with files or related material needed for meeting, correspondence, and reports;

- Maintains confidentiality of documents and information received;- Demonstrates a desire to address customer needs and does so in a

professional manner;- Communicates with other branches as for possible maintenance of

equipments and to seek technical assistance on the sport;- Respond to public inquires;- Keeps informed of office details and advises management of problems;- Determines needs and orders office supplies, equipment, repair and

maintenance services through the company’s channels and in effect enhancing the work at hand;

- operates standard office equipment;- Performs reacted work as assigned;Desirable - 2 years of experience specifically in the area of sales administration

in office equipment and maintenance trading company and/ or sales industry experience in customer-handling;

- Proven track record in a sales and customer service environment;- Computer literacy;

Additional Requirements

- The ability to work alone and be self-starter;- Friendly, with the ability to interact with colleagues and customers at all

levels;- Honesty, loyalty and trustworthiness with an attitude of constant

improvement; - Handling of customer queries when necessary;- ordering Stationery;Essential- Ability to communicate at all levels;- The ability to create a positive, everlasting impression with the most

professional, courteous and expedient manner and to continually strive for superior client service;

- An ability to work under limited supervision.- Proactive, punctual and reliable;- Well presented and spoken;- Vibrant nature;- Enjoys dealing with people daily and is tolerant of rude people, polite but

assertive.Interested applicants for the above posts can apply within 10 days starting from the day this vacancy is posted in our office located at Bole (in front of Millennium Hall; besides Bole Mini). When applying, applicants must bring along the necessary original credentials along with the copiesApplication letter and resume (CV) must be incorporated. Only short-listed applicants will be contacted.Please note that the work place for all positions is in Addis Ababa.Jupiter Trading is an Equal Employment Opportunity follower. Nepotism, in any form is highly disregarded within the company.

ማስታወቂያ

Page 22: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 22|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

Page 23: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 23 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

Saudi Arabian Airways is looking for Female Flight Attendant; exceptional people to join our international cabin crew team.Do you have what it takes to be part of our team?

The Saudi Airways cabin crew requirements are:• 22-30Years of Age at the time of joining,• English Language fluency (Spoken & Written); Additional Languages

are desirable• Arm reach of 212 cm while standing on tiptoes; Minimum height of

1,60m with weight in proportion to height: Physically fit to meet the Saudi Airways cabin crew requirements,

• Valid Passport which permits worldwide travel without restriction• Good Health• Minimum Level of education of High school diploma or equivalent.• Ability to relocate to various locations on worldwide bases for lengthy

periods.• Clear Speech, good hearing and eyesight (glasses/ contact lenses

are allowed).• Good swimming skills, be able to swim minimum 25, meters unaided.• Clean criminal record.• No visible tattoos, body piercing or dental braces (cosmetics &

bandage coverings are not permitted).

If you fulfill the above requirements please send your Resume, 1 scanned full length photographs (wearing business attire) & 1 scanned passport size picture through [email protected].

Job opportunity

ማስታወቂያ

Page 24: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 24|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

TERMS OF REFERENCE FOR MALARIA GLOBAL FUND CONSULTANT On

Malaria Vector Control

1 Background:

Malaria remains high on the list of diseases of public health importance in Ethiopia. About 75% of the land and 68% of the population are at risk of malaria infection. Transmission of malaria in the country is s unstable, often characterized by devastating epidemics.In recent years, Ethiopia has made significant achievement in expanding coverage of key malaria interventions throughout the country, the Major scale-up efforts began in 2004/2005 with the introduction of artemisinin-based combination therapy (ACT) as the first line treatment, then expanded use of Rapid Diagnostic Tests (RDT) as well as stepping up of vector control and prevention through the wide distribution of Long-Lasting Insecticidal Nets (LLINs) along with targeted Indoor Residual Spraying (IRS). The main aim for expanding access to these interventions was to achieve the objectives of the 2006-2010 five-year National Malaria Strategic Plan which is designed on the ‘Scale-up for Impact’ (SUFI) approach.Since the program been aggressively and successfully implementing the integrated scale up effort through support of the Global Fund and others partners, the country results remarkable improvement in-terms of malaria burden reduction.

2. Major Responsibilities of consultant:• Provide technical support to the Federal Ministry of Health on the implementation of vector

control interventions.• Provide technical support in all aspects of vector control interventions based on the national

vector control guideline.• Supporting the capacity building efforts of the program using relevant tools and approaches

for relevant stakeholders and program staff in various aspects of malaria control and related fields;

• Work closely with Ethiopian health and nutrition research institute (EHNRI) and partners on the insecticide monitoring (susceptibility and bio-assay tests).

• Actively participate in IRS and other vector control effort including insecticide resistance management, epidemic preparedness tasks.

• Participate and facilitate operational researches.• Liaise with research institutes and medical college and other related sectors on issues of

malaria vector issues.Accountability

• Consultants will be directly accountable to the FMOH, Agrarian Health Promotion and Disease Prevention (AHPDP).

Number of Consultant,

i. One malaria vector control expert 3. Working area and Duty Station

The consults will be based at Federal Ministry of Health: (Duty Station: Addis Ababa)4. Additional information

i. Salary: Salary is negotiable

ii. Qualification and Work experiences:-

Certified university degree , Masters degree in entomology or other closely related field of studies (BSc+MSc , MD+MSc, PHD) and individuals having 4 years and above experiences in public health and program Managementwith focus on malaria prevention and control program.

iii. Terms of employment: For one year with possible extension

iv. Interested applicants are invited to submit their non returnable applications, CVs and copies of all documents together with their original document within (10) days from the first announcement to:

FEDERAL MINISTRY OF HEALTHHUMAN RESOURCE DEVELOPMENT AND ADMI.

DIRECTORATEP.O.BOX: 1234

TEL: 0115-515425ADDIS ABEBA ETHIOPIA

Vacancy announcementFederal Ministry of Health

TERMS OF REFERENCE FOR MALARIA GLOBAL FUND CONSULTANT on Malaria Monitoring & Evaluation

1 Background:

Malaria remains high on the list of diseases of public health importance in Ethiopia. About 75% of the land and 68% of the population are at risk of malaria infection. Transmission of malaria in the country is s unstable, often characterized by devastating epidemics.In recent years, Ethiopia has made significant achievement in expanding coverage of key malaria interventions throughout the country, the Major scale-up efforts began in 2004/2005 with the introduction of artemisinin-based combination therapy (ACT) as the first line treatment, then expanded use of Rapid Diagnostic Tests (RDT) as well as stepping up of vector control and prevention through the wide distribution of Long-Lasting Insecticidal Nets (LLINs) along with targeted Indoor Residual Spraying (IRS). The main aim for expanding access to these interventions was to achieve the objectives of the 2006-2010 five-year National Malaria Strategic Plan which is designed on the ‘Scale-up for Impact’ (SUFI) approach.Since the program been aggressively and successfully implementing the integrated scale up effort through support of the Global Fund and others partners, the country results remarkable improvement in-terms of malaria burden reduction.

2. Major Responsibilities of consultant:i) Provide technical support to the Federal Ministry of Health on the implementation of

global fund supported malaria prevention and control activities ii) Conduct supervision, monitoring and evaluation activities iii) Coordinate and organize sensitization and social mobilization activitiesiv) Establish/ Strengthening database for monitoring and evaluation of project activitiesv) Participate in planning and evaluation meetings.vi) Assist in strengthening partnership development at all levels (Regional, Zonal, District

and community levels).vii) Ensure that target populations are actually benefited from the services.viii) Provide feedback to regions, zones, districts.ix) Brief regularly and submit monthly, quarter, biannual and annual written activity reports

to the FMOH.x) Perform other duties as required by FMOH.xi) Consultants will be directly accountable to the FMOH, Agrarian Health Promotion and

Disease Prevention (AHPDP).

Accountability• Consultants will be directly accountable to the FMOH, Agrarian Health Promotion and

Disease Prevention (AHPDP).

Number of Consultant,i. One monitoring & evaluation expert

3. Working area and Duty Station The consult will be based at Federal Ministry of Health: (Duty Station: Addis Ababa)

4. Additional information

i. Salary: Salary is negotiable

ii. Qualification and Work experiences:- Certified university degree in medicine , Masters degree in Public Health or other related field of studies (MD+MPH, MD+MSc, BSc+MPH, BSc+MSc, PHD) and individuals having 4 Years and above experiences in public health and program Managementwith focus on malaria prevention and control.

iii. Terms of employment: For one year with possible extension

iv. Interested applicants are invited to submit their non returnable applications, CVs and copies of all documents together with their original document within (10) days from the first announcement to:

FEDERAL MINISTRY OF HEALTHHUMAN RESOURCE DEVELOPMENT AND ADMI.

DIRECTORATEP.O.BOX: 1234

TEL: 0115-515425ADDIS ABEBA ETHIOPIA

ማስታወቂያ

Page 25: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 25 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

Hope for children organization is an indiginious NGO working for and with HIV/ADISaffected and infected sectors of the population in Gulele, Nifas silk lafto, Arada and Yeka in Addis Ababa Region and in Oromia Region Jimma Zone and Babile.HFC is seeking to recruit a higher capable professionals for the following positions. Job Profiles of the ESAP2 Core Grantee Team

1. Project Coordinator. A fulltime staff position, stationed at the Headquarter of Hope for Children

Major Duties and Responsibilities;

Plans, organizes, coordinates and guides the implementation of the project in all the intervention Woredas,

Provides technical and organizational support to the SA(Social Acountablity) implementation teams of the lead and sub-partner organizations,

Follows up and implements directives and guidelines of the project management team as per the contract with the MA,

Follows up timely disbursement of project funds and proper uses of the resources,Organizes, coordinate, implements and ensures the quality of trainings on SA for Woreda social

accountability staff and woreda officials and citizens groups,Organizes and conducts project monitoring visits,Consolidates and submits quarterlyprogress report to the Management Agency (MA) on Quarterly

basis as per agreed upon time frame and format, Ensure monitoring, evaluating and documenting progress of program implementation

against indicators and ensure that activities are on track ;Providing overall guidance and direction focusing the program team on achieving agreed

targetsPeriodically collect and prepare success stories and best practices; disseminate reports to

stakeholders Coordinate and conduct baseline and mid-term evaluations and dissemination for actionEnsures that the MA receives timely financial and technical reports that would allow the smooth

implementation of the project,Documents and disseminates studies, learning experiences and best practices in implementing

SA tools,Liaises with regional,zonal and woreda sector bureaus and departments on SA project matters;Serves as the secretary of the steering team

Required Qualification:MA/MSC Degree in Agriculture, Sociology, Economics, Education, Public Health, Social Work, Anthropology, and related fields with 4 years relevant experience or BA with 6 years of hands on experience in project management, program planning, monitoring and evaluation using participatory approaches and tools; communication and facilitation skills are also key qualities

2.Social Accountability Project Accountant (1):

Being full time worker and accountable to the Senior SA Project Coordinator he/she accomplishes the following:

Major Duties and Responsibilities:

Assist Project Coordinator for preparing budget plans, Liaise with the heads of finances of the lead partner, sub-partner and Management

Agency on the financial management aspects of the project Ensure that Programme expenditure figures reconcile with those held by the lead partner

and sub-partner/s; Conduct financial monitoring of the sub-partner so as to ensure the fund is properly

spent; Prepare periodical financial reports based on agreed time frame; Ensure the financial management is in line with the terms and conditions depicted in the

grant manual; Facilitate the periodic Project audit as required and submit the report to the MA; Responsible for the facilitation of any project administration with financial matters Carryout any other relevant duties as may be specified by the senior SA programme

coordinator

Required Qualification:BA Degree in Accounting with 4years relevant experience.

Duty Station:-Harar region ,Babile Zone,SNNPR ,Shebedino, Oromia Region ,Ejere Woreda,Sibusire,Bako Tibe

3. Woreda Social Accountability Project Coordinators (5): These are fulltime staff, to be stationed in each SA implementing Woredas and responsible for the overall organization, coordination and implementation of the SA project in their respective Woredas.Their task includes;

Major Duties & Responsibilities:

Preparing work plans of the Woreda SA project and implementation up on approval by the project management team

Attending training organized at various levels on social accountability tools and approaches and making sure that all other relevant staff attend these workshops

Organizing and leading the trainings for Woreda facilitators and community mobilizers; and woreda officials, service providers and citizens groups

Liaising with Woreda sector offices and administration and mobilizing support for the SA project

Liaising with community and citizens’ groups, associations and key community representatives to mobilize support for the SA project

Coordinating performance assessment surveys conducted using SA tools in the Woreda and in close collaboration with the SA project coordinator at the lead agency

Regular data collection and documentation of project activities and report to the project coordinator/Monitoring and Evaluation officer

In collaboration with the SA coordinator, conduct baseline and midterm review of the Social accountability program

Preparing and submitting quarterly narrative reports to the SA coordinator in the lead CSO as per agreed upon time frame.

Carry out any other relevant duties as may be specified by the Project Coordinator Serve as a frontline staff of the project to mobilize citizens groups, user communities

and service providers to participate in the different stages of the project, Implement activities of the project as per agreed up on plan of action, Organize and implement the selection of user community groups for the assessment of

services as per the project strategies and guidelines, Work with the selected service provider institutions in their sites and facilitate, as per

guidelines, self assessment of public services, Organize and facilitate service user-provider dialogue and action plans using SA tools, Ensure that the interests, demands and preferences of marginalized members of the

community, particularly Women, children, the elderly, the disabled and People Living with HIV/AIDS (PLWHAs) are taken into account in every aspect of the project design and implementation process,

Prepare and submit activity plans and performance reports to the Woreda SA coordinator as per agreed up on format and time frame.

Required Qualification:MA/MSC Degree in Agriculture, Education, Economics, Sociology, and related fields with 1 years relevant experience or BA/BSC with 2 years years relevant experience in participatory development work.

4. Monitoring and Evaluation Officer

• Provide technical leadership and support for monitoring and evaluation and knowledge management of the project.

• Ensure timely and complete reporting from the woreda level to the lead organization project coordinator (head office).

• Monitor and evaluate progress towards annual work plans, expected outputs, including selecting and monitoring progress in meeting indicators.

• Assist the Project coordinator in the preparation of work plans, refining of the logical framework, selection of indicators and annual implementation plans with a view towards the project’s M&E requirements.

• Coordinate the preparation of quarterly progress reports, annual project report, and success stories for the social accountability Program.

• Collect data for annual M&E plan and use those data to improve project performance.• Develop a detailed annual work plan to build technical and managerial capacity of its sub partner(s)

Required Qualifications: MA/MSC in Measurement and Evaluation, Economics, Sociology, and related fields with two years relevant experience or BA/BSC with four years relevant experience in participatory development work.

5. Translation Consultant (1):

The Amharic (or any other language) translator will be responsible for the following activities:

• Overall translation and editorial of the Social Accountability Guide from English into Amharic

which includes:

• Amharic editing of grammar, spelling and punctuation;

• Editing of the logic, coherency and flow of sentence structure in the Guide;

• Editing of the consistency of terminology across the Guide;

Required Qualifications: A Master degree in Amharic or Journalism or Education or related field; Ten

years or more experience in translation from English-Amharic and copy editing, especially in the context

of the development sector of Ethiopia; A proven track record in translation (English-Amharic), editorial

and copy editing, and examples should be provided; Expert knowledge and practice of the development

sector in Ethiopia; Fluency in English and Amharic written and spoken is an essential requirement.

6. Capacity Support or Social Accountability Tool Consultant(1):

• Review the selected proposals, action plans and logical frameworks of the grantee/s s/he will mentor and support;

• Assist the selected grantee/s and help develop a joint action plan that details the mentoring and support each of the grantees will receive;

• Assist in the development of a support plan for the core staff on one or more of the social accountability tools

Salary: - as per the organization Scale

Apply to: - Hope for the Children Organization

P.O.box 24550 code 1000

Tel.0111 22 26 21

Dead line: - 10 days after this Anouncement

Address: - Arat Kilo /Ginfle on the way to Addis Maternity and Children Hospital.

ማስታወቂያ

Page 26: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 26|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

Construction and Business Bank S.C. would like to invite competent and qualified applications for the following positions.

የኮንስትራክሽንና የቢዝነስ ባንክ አ.ማConstruCtion & Business Bank s.C

1. Branch Manager –I • Vacancy No. 250

Educational Qualification and Work Experience:-• Bachelor Degree in Accounting, Accounting & Finance, Banking & Finance, Management,

Economics or business related field and after holding BA 3 years of Bank Experience as Customer Relationship Officer or Senior Customer Service Officer or Branch Controller. Or

• Diploma in Accounting, Management, Economics or business related field and after holding Diploma 6 years of Bank Experience as customer Relationship Officer or Senior customer Service officer or Branch Controller.

Required Competencies and Specificationo Strong ability to communicate clearly both orally and in writingo Good interpersonal skillso Ability to lead and coach others o Take initiative and set prioritieso Acting with integrityo Flexible and adapt to new business needso Computer literateo Knowledge in service marketing

Job Location :- BONGA AND BABILE BRANCHES 2. Customer Service Manager –I

• Vacancy No. 251Educational Qualification and Work Experience:-

• Bachelor Degree in Accounting, Accounting & Finance, Banking & Finance, Management, Economics or business related field and after holding BA 2 years of Bank Experience as Customer Relationship Officer or Senior Customer Service Officer or Branch Controller. Or

• Diploma in Accounting, Management, Economics or business related field and after holding Diploma 5 years of Bank Experience as customer Relationship Officer or Senior customer Service officer or Branch Controller.

Required Competencies and Specification• Ability to work in team• Ability to manage works without supervision• Demonstration of strong personal commitment to learn particular skill • Good interpersonal skills i.e. courtesy for customers and good communication skill• Acting with integrity • Flexible and adapt to new business need• Knowledge of basic computer applications• Conflict management skill• Certified in the banking applications software• Good knowledge of bank accounting • Knowledge of basic service marketing techniques

Job Location :- BABILE, METU, BONGA, JINKA, YIRGALEM,TEPI AND DEBRE BIRHAN BRANCHES

3. SENIOR COLLATERAL VALUATOR( Senior Engineer)

• Vacancy No. 252•Educational Qualification and Work Experience:-

Degree in civil engineering, Building Construction Management, with 4 years Engineering Experience.

Required Competencies and Specification • Property valuation knowledge and skill;• Knowledge of valuation procedure; • Technical advisory skill;• General banking operation knowledge;• Computer skill;• Working in teams, cooperation and commitment;• Self learning and improving and openness to change;• Self –starter;• Willingness to work under stress and meet deadlines;• Honesty and integrity; Job Location :- Head Office

4. COLLATERAL VALUATOR CHECKER• Vacancy No. 253•Educational Qualification and Work Experience:-

Diploma in Mechanical Engineering and 5 Years Engineering Experience, out of which 2 years’ experience in related works.

Required Competencies and Specification • Property valuation knowledge and skill.• Knowledgeof valuation procedure.• Knowledge of market price of the collateral properties.• Computer skill.• Working in teams, cooperation and commitment;• Passionate for results.• Self learning and improving and openness to change.• Willingness to work under stress and meet deadlines.

Job Location :- Head Office5. Junior Officer Vacancy No. 254

Educational Qualification: First Degree in Accounting /Business Administration/ Finance & Development Economics / Banking & Insurance /Marketing Management/ Management/ Economics and other related field.

Competency (Knowledge, skills and abilities)

• Ability to work in team • Good interpersonal skills i.e. courteous and good communication skill• Acting with integrity • Comply with the Banks’ Code of Ethics• Knowledge of basic Computer applications

Work Experience: Not Required

Graduation Year: 2002- 2005 E.C Graduates

CGPA: 2.75 and above

Other Required Skill: knowledge of Basic Computer Application is Preferred.

Job Location :- Addis Ababa

6. Office Assistant

Vacancy No. 255

Educational Qualification: - Diploma in Secretarial Science & Office Management

Work Experience: Not Required

Competency (Knowledge, skills and abilities)

•Good knowledge of office management practices

•Good inter-personal skills

•Ability to coordinate and administer office activities

•Ability to compose letters and memorandums

•Ability to operate office equipment such as Fax and Photocopier

Graduation Year: 2002 - 2005 EC Graduates

CGPA: 3 or above an average of 80 %

Salary : As per the Bank’s Scale

Other Required Skill: knowledge of Basic Computer Application is Mandatory.

For all position :-

Term of employment; _ Permanent

Salary: - as per Bank’s scale

Application Procedure Interested and qualified applicants are invited to submit their Application, Curriculum Vitae, copy and Originals of Credentials and Documents related to education and work experience to Construction & Business Bank – Human Resource Management Process at our Head Office located in front of Addis Ababa University Collage of Commerce.

Tel:- 0115 15 27 25, 0115 52 38 49

Closing Date of Application: Within 5 (Five) Working Days from the date of this announcement..

Page 27: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 27 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ማስታወቂያ

ኢምፓየር አዲስ ኢንተርናሽናል ሆቴል ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

የሥራ መደቡ መጠሪያ፡- የሰው ሃብት አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ

ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ በማኔጅመንት ወይም በተመሳሳይ የትምህርት

መስክ በዲግሪ የተመረቀ

የሥራ ልምድ በተመሳሳይ ስራ በታወቀ ድርጅት ውስጥ 4

ዓመትና ከዚያ በላይ ያገለገለ ቢቻል

በትልልቅ ሆቴል የሰራ

ብዛት አንድ

የሥራ ቦታ አዲስ አበባ

ደሞዝ በስምምነት

መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ7(ሰባት) የስራ ቀናት ውስጥ የማይመለስ የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃ ኮፒ ጋር በመያዝ ዘወትር በስራ ሰዓት ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ለበለጠ መረጃ፡- ስ.ቁ 0116188766/0116614524

አድራሻ፡- ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ ፊት ለፊት፣ ከአምባሳደር ሆቴል በስተጀርባ፣ 150

ሜትር ገባ ብሎ

Gender in Humanitarian Action Working Group

Call for Consultancy Services To develop Gender Policies and Gender Mainstreaming Guidelines for Local

Humanitarian Non-government Organizations

The Gender in Humanitarian Action Working Group (GHAWG) was established in 2010 by international humanitarian NGOs operating in Ethiopia with the aim of enhancing effective gender mainstreaming in humanitarian responses. A small working group composed of Oxfam GB, CARE Ethiopia, Child Fund, GOAL Ethiopia, CONCERN Worldwide and CCRDA was formed out of the large working group to steer this initiative and provide technical support for future collaborations. The ultimate purpose of the group is to ensure gender mainstreaming in humanitarian responses through establishing common tools and standards; revisiting organizational policies and internal practices; building the capacity as well as accountability of member organizations, partners and government stakeholders. To attain these, the project entitled: ‘Integrating Gender Standards in Humanitarian Action’ has been initiated as a combined effort through the coordination of Oxfam GB.

Under this project, the working group would like to support the capacity development of local humanitarian NGOs on gender mainstreaming practices through developing tailored gender policies and mainstreaming guidelines.

Therefore, the working group is seeking to hire three consultants/firms to develop gender policy and gender mainstreaming guideline to local humanitarian NGOs. The consultants/firms are expected to provide highly qualified multi-disciplinary professionals with relevant work experience to the task at hand. The consultants are expected to have a minimum of MA degree in Gender Studies, Social Work, Rural Development or related fields of study with at least 8 years of work experience in gender related interventions. The consultants/firms should have practical work experience on gender auditing, policy development, gender research and developing gender standards and tools with strong and demonstrable prior experience of delivering high quality works. The consultants/firms are also expected to keep the gender balance of the team they propose for the task.

Important note: The candidates/consultancy firm applying for this research should have a Tax Identification Number (TIN). Submission: Interested consulting firms can collect the TOR prepared for the assignment from the Oxfam GB country office located at Megenagna – Bole Ring Road near Imperial Hotel next to DHL Head Office -Bole Kifle Ketema, Kebele 08/09 House No. 1419 Telephone: +251-116-613344 starting from Monday, 13 December 2012 and submit their separate technical and financial proposals for each task along with the relevant credentials by Wednesday, 26 December 2012 before 4:00 PM.

The Bid will be opened on 25 December 2012 at 10:00 AM at Oxfam GB Addis Ababa Office.

Go4goal International Job Relation Agency The following listed applicants are passed the written exam. So please report to our organization with in 5 working days of this anouncement.

Nursing Laboratory Druggist1 Abiot Mesfin 14 Yewondowosen Mengistu 1 Eleni Dagne 1 Abreham Tsegaye 10 Tatek Dinberu2 Girma Moges 15 Samuel Ibrahim 2 Hiwot Tesfaye 2 Nigatu Teshager 11 Mesafinet Mersha3 Martha H/Mariam 16 Hawi Gemechu 3 Kemeriya Awel 3 Degie Wale 12 Aselefech Mekuria4 Samrawit Assefa 17 Zelalem Gemechu 4 Yonnes Ashene 4 Hiwot Abebe 13 Etsehiwot Menberu5 Eskedar Andualem 18 Fikirte Girma 5 Eden Rocket 5 Eliyas Getachew 14 Degi Gutema6 Kiros Bihonegne 19 Eskedar wordofa 6 Mohammed Ali 6 Heirut Wubshet 15 Asnake Balcha7 Zemzem Ali 20 Biniyam Kassahun 7 Tarekegne Gofa 7 Solomon Girma 16 Solomon Abera8 H/Marim Kassaye 21 Senait Dansa 8 Belete Tufer 8 Tamirate w/Giorgis 17 Elsabeth Mekonene9 Sophia Shifa 22 Zulfa Jemal 9 Tsehay Nega 9 Martha Getachew 18Fekadu Merga10 Geleta Leta 23 Selamawit Solomon11 Zimale Melkamu 24 Abezaw Abebe12 Henok Metaferiya 25 Tigist Mesganaw13Tesfu Atsebeha

Health Officer &Public Nurse Midwife Accounting1 Hiwot Hunde 14Tedeso Bonga 1 Nigatu Fikadu 1 Yared Girma 16 NetsaneAweke 15 Fufa Teferi 2 Rehima Mohammed 2 Mesret Abebe 17 Eskedare Tadese3 Getahun Hailu 16 Tolcha Kenenu 3 Tigist Worku 3 Natnael Hadgu 18 Merima Enda4 Delinesaw Teshome 17 Tsehayenesh Biru 4 Selamawit Bedawi 4 Etaferaw Biru 19 Kemeria Awel5 Balemlay Tiruneh 18 Kiros W/Mariam 5 Fantaneh Tigabu 5 Zeleke Metaferia 20 Abonesh Tola6 Tadele Tibebu 19 Samson Mitiku 6 Zelalem Mihretu 6 Yonatan Tolosa7 Kelemu Tilahun 20 Ketema Semahegne 7 Anteneh Bekele 7 Yenenesh Kefyalew 8 Sifan Nemera 21 Hiwot Demoze 8 Mergia Feleke 8 Atsede Kibret 9 Senait Awel 22 Abdu Mussema 9 Bekalu Tegegnu 9 Wolde Tesema10 Meskele Shumet 23 Melese Tafese 10 Genet Abera 10 G/Libanos Kassaye11 Fozia Kemal 24 Kelemu Oljira 11Tigist Tesfaye 11 Nigatu Getaneh12 Kedir Toffic 25Yodit Zeleke 12Kebede Getu 12 Meskerem Tesfaye13 Habtom Kifle 13 Helen Messay 13 Henok Alemu 14 Tsion Takele 14 Yohannes Tarekegne 15Eleni Ameh 15 Mesfin Kebede

Open Vacancies on Addis Ababa and Regional States * Radiologist (Sal. 40,000 birr) * Nurse (Sal.1,000-3,500 birr) * Surgeon (Sal.35,000 birr) * Laboratory (Sal.1,000-3,000 birr)* Internist (Sal.35,000 birr) * Pharmacy (above 5 year experience)(Sal.4,000-7,000 birr)* Pediatrician (Sal.30,000 birr) * Midwifery (Sal. 2,500-4,000 birr)* G.P (Sal.12,000 birr) * Health Officer (Sal.1,500-8,000birr) * X-ray Technician & Technologist (Sal.3,000-9,000 birr) * Dental Professional (Sal. 5,000-12,000 birr)

Telephone:- 251 11 5 53 00 25 For daily vacancies you can Visit our web site www.gogoaljobs.com Address: from Mexico to kera road Tsilere Building 3rd floor Office No. 2A, 2B

Page 28: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 28|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

Vacancy AnnouncementPosition Minimum Educational Background Total years of Experience

In Civil WorksWork Experience inSmilar Assignment in Road/Bridge

Projects

Location

Resident Engineer BSc. Degree in Civil Engineering 10 6 ProjectAssistant Resident Engineer BSc. Degree in Civil Engineering 8 4 ProjectCADD Engineer/Designer BSc. Degree in Civil Engineering/Diploma 4 3 Head OfficeAutoCAD Technician Diploma/Certificate 5 3 Head Office

Quantity SurveyorBSC Degree in civil Engineering 6 3

ProjectDiploma in Civil Engineering 8 4Certificate from Technical School 10 4

Senior Surveyor Diploma from Technical School 12 8 ProjectStructural Inspector BSc. Degree in Civil Engineering 3 3 ProjectMaterial Inspector Technical Diploma 5 5 ProjectWork Inspector Certificate from Technical School 7 7 ProjectSurveyor BSc. Degree in Civil Engineering 3 3 Project

Technical Diploma 10 7Drafts Person BSc. Degree in Civil Engineering 3 3 Head Office

Diploma, Technical School 5 5Structural Engineer BSc. Degree in Civil Engineering 6 3 ProjectMaterial/Pavement Engineer BSc. Degree in Civil Engineering or similar field 6 4 Project

0116 47 65 48

0116 47 82 52/53

IMMEDIATE VACANCYBOKRA Construction and Trading Plc would like to invite competent candidates for the following positions.

S/N Title Qualification Experience Location Quantity

1 Project Manager BSC in civil Engineering 5 Years Project 5

2 Project Engineer Advance Diploma in civil Engineering/Building Engineering4/6 Years

›› 5

3 Office Engineer Advance Diploma in civil Engineering/Building Engineering 6 Years ›› 3

4 Quantity Surveyor Advance Diploma in civil Engineering/Building Engineering 4 Years ›› 3

5 Surveyor Diploma in surveying 4 Years ›› 3

6 Junior Surveyor Diploma in surveying 2 Years ›› 8

7 General Forman Diploma in Construction Technology 6 Years ›› 10

8 Equipment & Machinery Division HeadAdvance Diploma in Mechanical Engineering/ Auto mechanics

6 Years Head Office

1

9 Mechanic Diploma in Auto / General Mechanics 4 years Project 3

10 Accountant Diploma in Accounting 2 years

›› 3

11 Logistic officer Diploma in Management 2 Years ››

3

Salary: Negotiable Interested qualified applicants are advised to apply in person or B.O. Box 46526, by attaching their non-returnable application and CV with all credentials within Ten Working days of this announcement. Address: BOKRA Construction & Trading PLC. Bole Sub City Woreda 14, Gerji (in front of Unity University) Telephone No. 0118-962760 Addis Ababa

ቦክራ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበርBokra Construction and Trading PLC

VACANCY ANNOUNCEMENTNasew Construction plc would like to invite competent and self-motivated job applicants for the following vacant positions:

S/N Position EducationWork experience in

Additional Skill Req. qty Work place

General Particular

1 Project Coordinator B.Sc. in civil Engineering 8 years 4 years at project MS-WordMS-Excel 1 Addis Ababa

2 Office Engineer B.Sc. in civil Engineering 6 years 4 years as office engineer

AutoCAD MS-Project 1 Addis Ababa

Interested applicants who fulfill the above requirements can submit their application, detailed CV and non-returnable copies of their credentials within 7 calendar days to the following address: Address:- Nasew Construction plc Gottera, infront of Pepsicola Factory P.O.Box 8826, Addis Ababa Tel. 0114-426215, 0114-423026 Fax: 0114-424420Salary:- Attractive & Negotiable

Page 29: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 29 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

- ጤና ይስጥልኝ እንዴት ናችሁ? እንኳ ደህና መጣችሁ::

- ጤና ይስጥልኝ እንዴት ነህ? ቅድም ከሩቅ ሳይህ’ኮ ኢትዮጵያዊ ይመስላል ብለን እየተነጋገርን ነበር::

- እኔም አይቻችሁ ነበር፤ ግርግሩ ሲበዛ በዕረፍት ጊዜ አገኛችኋለሁ ብዬ ነው እንጂ::

- ዳያስፖራም እንደዚህ ያስባል እንዴ?

- እንዴት ክቡር ሚኒስትር?

- ማለቴ ዳያስፖራው እኛን ሲያይ ሠልፍ የሚወጣ እንጂ ሰላምታ የሚለዋወጥ አይመስለኝም ነበር::

- እንደዚያ ዓይነቶችም አሉ ግን ጥቂቶች ናቸው’ኮ:: ብዙ ጥሩ ኢትዮጵያዊያን አሉ:: እነሱን እያያችሁ ሁሉም እንደነሱ አይምሰላችሁ::

- ቅድም ጥሩ ሐሳብ ነበር ያቀረብከው:: ጥሩ ምክር ነበር የሰጠኸው:: ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህን ያህል ጥሩ ምክር የምትሰጥ ከሆነ፣ ለአገርህስ ለምን ይህን ዓይነቱን ሐሳብና ምክር አትሰጥም?

- ልዩነት አለ ክቡር ሚኒስትር::

- በእኛና በእነሱ መካከል ልዩነት አለ?

- አዎን አለ::

- የምን ልዩነት?

- እነሱ ያዳምጣሉ እናንተ አታዳምጡም::

- እ… እናዳምጣለን እንጂ ሐሳብ ሰጥተኸንና መክረኸን አናዳምጥም ያልንበት ተጨባጭ ሁኔታ አለ? ወይስ አያዳምጡም ሲባል ሰምተህ አንተም አሉታዊ ድምዳሜ ላይ ደርሰህ ነው?

- ክቡር ሚኒስትር እኔ አሉታዊ መንፈስ የለኝም:: አላዳምጥም ብትሉም በተደጋጋሚ እሞክራለሁ እንጂ ተስፋ አልቆርጥም:: እዚህ ሁነው አሉታዊ ወሬ የሚያወሩትን አልሰማቸውም አልቀበላቸውም:: እታገላቸዋለሁ እንጂ::

- አማካሪ ሆነው የሚሠራ ከዳያስፖራው እናመጣለን፤ እንዴት አታዳምጡም ትለናለህ?

- ይኼውልዎት ክቡር ሚኒስትር፤ ተቀጥሮ ስለሚሠራ ዳያስፖራ ወይም ባለሙያ አይደለም እየተናገርኩ ያለሁት::

- ስለማን ነው የምታወራው ታዲያ?

- ሳይቀጠርም ዳያስፖራም ሆኖ አገር ውስጥ የሚኖርና ጥሩ ዕውቀትና ልምድ ይዞ እንደ ዜጋ፣ እንደ ምሑርና እንደ ባለሙያ በመቆርቆር ሐሳብና ምክር ለሚሰጥ መድረክ አትከፍቱም:: ሐሳብ ስለማትቀበሉም አታዳምጡም ነው እያልኩ ያለሁት::

- የእኔ መሥሪያ ቤት ባይሆንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዳያስፖራ ስብሰባ ይጠራል፤ ሐሳብ ስጡ ይላል:: አሁንም እያጠናከረው ነው ግንኙነቱን::

- አውቃለሁ ስብሰባ ይካሄዳል:: መሬት ይሰጠን፣ ጉምሩክ ላይ አትፈትሹን፣ ወዘተ የሚል ሐሳብ ይቀርባል:: እኔ እያሰብኩ ያለሁት ከዚያ በላይ ነው::

(የሻይ ዕረፍት አልቆ ስብሰባው ሲቀጥል በኋላ ምሳ ላይ እናወራለን ብለው ተለያይተው ነበርና እንደገና ለምሳ አብረው ተቀመጡ)

- እሺ እኔ የምለው ያለሁት ከዚያ በላይ ነው ብለህ ነበር ያቋረጥከው:: ከዚያ በላይ ምን ታስባለህ?

- ክቡር ሚኒስትር እኔ በፖሊሲ ደረጃ ሊቀመጡ፣ ሊሰፍሩ፣ ሊቀየሩና ሊሻሻሉ ስለሚችሉ ጉዳዮች ነው እያሰብኩ ያለሁት::

- የምን የፖሊሲ ሐሳብ?

- ብዙ ሐሳብ አለ:: ለምሳሌ ዳያስፖራ ኢትዮጵያዊያን በሚመለከት ጠንካራና ጠቃሚ ፖሊሲ ሊወጣ ይችላል::

- እዚህ ያለውን ጽንፈኛ ተቃዋሚ ዳያስፖራ ለመያዝ ሲባል ፖሊሲ አውጡ እያልከን እንዳይሆን::

- ክቡር ሚኒስትር እባካችሁን ስለእነሱ

ተውት:: እነሱ ኦባማ ኢትዮጵያን ይደግፋል ብለው ኦባማን አትምረጡ ይላሉ:: ሱዛን ራይስ በቀብር ጊዜ ስለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ መልካም ጉዳዮችን ተናግራለች ብለው ከሥልጣን ትወረድ ይላሉ:: ዛሬ እዚህ ስብሰባ ውስጥ እናንተን በፈገግታ ያናገረውን አሜሪካዊና አውሮፓዊ ነገ ይሰድቡታል:: እናንተ ዘንድ የሚሠራ አትክልተኛ፣ የካፌና የሬስቶራንት ሠራተኛና ታክሲ ነጂ ሁሉ ለእነሱ ጠላት ነው:: እየተናገርኩ ያለሁት ስለነዚህ አይደለም::

- ስለማነው ታዲያ የምታወራው? ፖሊሲ ይስተካከል ይለወጥ እያልክ አይደል?

- ክቡር ሚኒስትር በጤና፣ በፋይናንስ፣ በኢንጂነሪንግ፣ በኮንስትራክሽን፣ በኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ፣ በዲፕሎማሲ፣ በሚዲያ፣ በንግድ፣ በኢንዱስትሪና በተለያዩ ዘርፎች ሙያ ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ለአገራቸው እንዲሠሩ የሚያግዝ አበረታችና ደጋፊ ፖሊሲዎች አውጡ አሳትፉ ነው እያልኩ ያለሁት::

- እ…

- በሁሉም መስኮች ዕውቀት ያላቸውን ለአገራቸው ጥቅም እንዲውሉ ማድረግ የሚችል አሠራርና አመራር ይኑር ማለቴ ነው::

- የዳያስፖራውን ዕውቀት ተጠቀሙ እያልክ ነው አይደል?

- አዎን ክቡር ሚኒስትር! እነ ጃፓንና ደቡብ ኮሪያ የበለፀጉት’ኮ ማዕድን ወይም ሌላ ሀብት ስላላቸው አይደለም:: ሀብታቸው የሰው ኃይል ነው:: ሀብታቸው ዕውቀት ነው:: የዜጎች ሙያ፣ የዜጎች ዕውቀት፣ የዳያስፖራ ዜጎች ልምድና ዕውቀት የትም ይኑር የትም ተጠቀሙበት በልፅጉበት::

- እህም ገባኝ፤ ግን ዳያስፖራውስ ዕውቀቱን ለአገር ጥቅም ለማዋል ዝግጁ ነው?

- ክቡር ሚኒስትር ጥሩ አሳታፊና ጠቃሚ ፖሊሲ ከወጣ ለራሴ ብሎ ነው የሚያደርገው:: 20 በመቶው ብቻ እንኳ እሺ ቢል ከበቂ በላይ ነው:: እርግጠኛ ነኝ ጽንፈኛውንና የጠላት መሣሪያ የሆነውን ትተን ሌላው ግን አገሩን ለማገልገል ይፈልጋል::

- ኢሕአዴግን ይወዳል ብለህ ነው?

- እንዴ! እንዴ! ክቡር ሚኒስትር እኔ እየተናገርኩ ያለሁት ኢሕአዴግን ስለመውደድና አለመውደድ፣ ኢሕአዴግን ስለመደገፍና አለመደገፍ አይደለም:: ሕግ እስካለ ድረስ ኢሕአዴግን መውደድም አለመውደድም መብት ነው:: መደገፍም አለመደገፍም መብት ነው:: ዜጋ ለአገሩ አስተዋጽኦ የሚያበረክተው ገዥውን ፓርቲ ሲደግፍ ብቻ አይደለም:: ሕግ ካልጣሰ ልዩነቱን ይዞም ለአገሩ ሊሠራ አገሩን በመጥቀም ሊያሳድግ ይችላል:: ስለፖለቲከኞች አይደለም እያወራሁ ያለሁት ስለዜጎች ነው::

- ገባኝ አመፀኛና ሽብርተኛ ካልሆነ መኖርና መሥራት ይችላል::

- ስለ ተራ መምረጥና ተራ መሥራት አይደለም እያወራሁ ያለሁት:: በዕውቀት፣ በሙያና በልምድ አገሩን የበለፀገችና ያደገች እንድትሆን ማድረግ ስለሚችለው ወገን ነው እየተናገርኩ ያለሁት::

- ገባኝ ጥሩ ሐሳብ ነው::

- ይህን ካሉ አዳመጡኝ ማለት ነው?

- ይህን ያላለ አላዳመጠም ማለት አይደለም::

- አሁን ያሉትንም እቀበለዋለሁ:: ኢሕአዴግ ድብቅና ሚስጥረኛ ነው ይባለ የለ?

- አንተም እንደነሱ ተቃዋሚ ነህ ልበል?

- እነሱ’ኮ ተቃዋሚዎች አይደሉም:: ተሳዳቢዎች እንጂ:: ቢቃወሙ ኖሮማ እወዳቸው ነበር::

- ኢሕአዴግን የሚቃወም ትወዳለህ ማለት ነው?

- ክቡር ሚኒስትር እውነተኛ ተቃዋሚዎች ከሆኑ’ኮ አማራጭ ያመጣሉ፤ ይመራመራሉ፤ የሚቃወማቸውንም

ያከብራሉ፤ ያዳምጣሉ ማለቴ ነው:: የእነዚህ’ኮ ስድብ፣ ጩኸት፣ የሻዕቢያ መሣሪያ መሆን፣ ወዘተ ነው:: ከኢትዮጵያ ጋር አትገናኙ፤ ኢትዮጵያን አትርዱ፤ ኢትዮጵያ አደገች አትበሉ፤ ያደገችው ኤርትራ ናት በሉ ነው የሚሉት:: መቃወምማ ያስከብራል:: እኔን ጩኸትና ስድብ ነው ያስጠላኝ:: በተለይ በተለይ በተቃውሞ ስም የጠላት መሣሪያ መሆን::

- በኢትዮጵያ አየር መንገድ አትብረሩ ማለት::

- ‹‹በኤምሬትስ አየር መንገድ ይሻላችኋል›› የሚል ኢትዮጵያዊነት::

- ተግባባን::

- መወያየት ለመግባባት በር ይከፍታል ክቡር ሚኒስትር:: ተወያዩ፣ አትራቁ፣ አትሽሹ፣ በጭፍን አትፍረዱ፣ አትፈርጁ::

- ጥሩ ኢትዮጵያዊ ነህ፤ በእውነቱ እንዳንተ ዕውቀትና ብስለት ያላቸውን በማሰባሰብ ምከራቸው::

- ክቡር ሚኒስትር ከእኔ በላይ ብዙ ዕውቀትና ልምድ ያላቸው አሉ:: እንዳሉ ስለማውቅ ነው ደፍሬ እየተናገርኩ ያለሁት:: በአሜሪካ በኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ የተሰማሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን አሉ:: በኤርፖርቶች ሴኩሪቲ ሥራ፣ በቦይንግ፣ በማይክሮ ሶፍት፣ በሌላም ሌላም ብዙ ባለሙያዎች አሉ:: በአሜሪካ ባንኮች በርካታ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች አሉ:: የዶክተሮች ብዛት ለጉድ ነው:: በፋይናንስ ሴክተር መዓት ናቸው:: በፋሽን በዲዛይን ዘርፍ ሳይቀር ሞልተዋል:: ክቡር ሚኒስትር እንጠቀምባቸው::

- አሰባስባቸው::

(ስብሰባውም በጥሩ ሁኔታ ተጠናቀቀ:: ከዳያስፖራው ኢትዮጵያዊ ጋር የተፈጠረው ግንኙነትም በእጅጉ ሁላቸውንም ያግባባና ያስደሰተ ነበር:: ክቡር ሚኒስትሩና አማካሪያቸው ወደኢትዮጵያ ከመመለሳቸው በፊትም አዲሱ ወዳጃቸው በቤቱ ራት ጋበዛቸው)

- ቆንጆ ቤት ነው:: ይህን የመሰለ ቤት ትታችሁ እውነት ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ትፈልጋላችሁ?

- ክቡር ሚኒስትር የሰው አገር ምን ጊዜም የሰው ነው:: አገርን የመሰለ የለም:: ሁለተኛ ደግሞ ወደ አገራችን እንመለስ ስንል አሜሪካና አውሮፓን እንተው ማለት አይደለም:: ሁለቱም ጋ እየኖሩ አገርን መጥቀም ይቻላል::

- ድሮ አሜሪካ ስመጣ ሰው ሁሉ የሚጋብዘው ሬስቶራንት እየወሰደ ነበር:: አሁን ቤትህ ውስጥ መጋበዝህ ጥሩ ነው::

- ቤቴንም እንዲያዩና ቤተሰቤንም እንዲተዋወቁ ብዬ ነው:: በየሬስቶራንቱ ደግሞ ጥሩ ሰው እንዳለ ሁሉ መጥፎ ሰውም አለ:: ካልተሳደብኩና ካልጮሁኩ የሚል:: ልጋብዝ ብዬ ላሰድብዎት አልፈልግም::

- ላንተም ጥሩ አይደለም::

- ለእኔማ ምን ችግር አለው?

- ከኢሕአዴግ ጋር ታየ ብለው አላስቀምጥ ይሉሃል::

- እውነቱን ልንገርዎት ክቡር ሚኒስትር ለእኔ ምንም ልዩነት የለውም:: አይረበሹኝም! አያስፈሩኝም! አይገርመኝም:: አሁንም እንሂድ ካሉ ወደ ሬስቶራንት መሄድ እንችላለን:: እኔም ወደነሱ አልወርድም፤ እነሱም ወደኔ መውጣት አይፈልጉም:: በእኔ ላይ ለውጥ አያመጡም::

- ጠንካራ ነህ ማለት ነው::

- እኔ ጠንካራ ስለሆንኩ ሳይሆን እነሱ በእጅጉ ስለወረዱና ስለተዳከሙ ነው::

- በደንብ አውቀሃቸዋል::

- ባለቤቴን ተዋወቁ ክቡር ሚኒስትር::

- እንዴት ነሽ ደህና ነሽ? እዚህ ስለጋበዛችሁን እናመሰግናለን:: ቆንጆ ቤት፣ ቆንጆ ቤተሰብ፣ ቆንጆ ልጆች::

- ግብዣችንን ተቀብላችሁ ስለመጣችሁ አመሰግናለሁ::

- ኢትዮጵያ ስትመጡ ብድራችንን እንከፍላለን:: ወይስ ከማይመጡት ዳያስፖራዎች ውስጥ ነሽ?

- በገዛ አገሬ ደግሞ ማን ይከለክለኛል?

(ግብዣው ተጠናቅቆ ተሰነባብተው ሊሄዱ ሲሉ ሚስትየዋ ለወላጆቼ አንድ ሺሕ ዶላር ውሰዱልኝ ብላ ተማፀነችና በዚህ ዙሪያ ውይይት ተከፈተ)

- ችግር የለም እንወስድልሻለን እንሰጣቸዋለን::

- አንድ ሺሕ ዶላር በብር ስንት መሆኑ ነው?

- አሥራ ስምንት ሺሕ ብር መሆኑ ነው::

- በጥቁር ገበያማ ከሃያ ሺሕ ብር በላይ ይደርሳል አሉ::

- እንግዲህ እኛ በዶላር መስጠቱ ላይ እንተባበራለን እንጂ መመንዘሩ ላይ የለንበትም:: እንዲሁም ጥቁር ገበያ ሕገወጥ ስለሆነ በባንክ መንዝሩት በሉዋቸው:: አቶ ባል በዚህ ዙሪያ ምን ትላለህ?

- በዚህ ዙሪያም የኢትዮጵያ መንግሥት ትልቅ የፖሊሲ ስህተት እየፈጸመና አገሪቷን እየጎዳ ነው እላለሁ::

- ም… ን?!!

- አዎን ክቡር ሚኒስትር ትልቅ ስህተት እየፈጸመ ነው::

- ምን የሚሉት ስህተት?

- ሰው ዶላር በባንክና በሕጋዊ ተቋማት ሲመነዝር የሚያገኘው ይቀንሳል፤ የአገልግሎት ክፍያውም ከፍ ይላል:: በጥቁር ገበያ ግን የበለጠ ይጠቀማል::

- እናም በዚህ ምክንያት ሰው ወደ ጥቁር ገበያ ይሄዳል ማለት ነው?

- እሱ ብቻ አይደለም ክቡር ሚኒስትር ጉዳቱ ከዚህም በላይ ነው::

- ሌላ ምን ጉዳት አለው?

- በጥቁር ገበያ የተመነዘረው ዶላር የት ይገባል? የት ይሄዳል? የሚለውን ጥያቄም መመለስ ያስፈልጋል::

- እነሱም’ኮ ዞሮ ዞሮ ባንክ ሄደው መመንዘራቸው አይቀርም::

- አይሳሳቱ ክቡር ሚኒስትር መንግሥትም አይሳሳት::

- እንዴት? አልገባኝም?

- በጥቁር ገበያ የተገኘ ዶላር በኢትዮጵያ ውስጥ ባንክ ሳይገባ ወደ ውጭ እየወጣ ነው::

- ማን ነው የሚያወጣው?

- ይወጣል ነው ቁምነገሩ እንጂ ቻይናዊያን ያወጡታል፤ ህንዳዊያን ያወጡታል፤ ኢትዮጵያዊያን ያወጡታል እያሉ መዘርዘር ይቻላል::

- እ…

- የዚህ ጉዳት ምን እንደሆነ ያውቃሉ ክቡር ሚኒስትር?

- ንገረኛ::

- ከዳያስፖራ ኢትዮጵያዊያን ወደ ቤተሰብ የሚላከው ገንዘብ ባንክ ካልገባ የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ክምችትን ለማሳደግ ሚና አይኖረውም::

- እንዴት አይኖረውም?

- ዶላር እየተባለ በጥቁር ገበያ ይመነዘራል:: ዶላሩ ይወጣል ባንክ አያውቀውም::

- በሌላ አገርስ?

- በሌላ አገርማ በርካታ የውጭ ምንዛሪ ፈቃድ ያላቸው ተቋማት አሉ:: የአገልግሎት ክፍያቸው አነስተኛ ነው:: ፈቃድ ያገኙት ባንክ እንዲያስገቡ ስለሚገደዱ ይጠቅማሉ:: አገር ውስጥ የገባ ዶላር አገር ውስጥ ይቀራል:: የውጭ ምንዛሪ ክምችትን ያሳድጋል:: የእኛ ገባ ይባላል፤ ከዚያ ይወጣል፤ አይከማችም:: ባንክ መሄድን ከማበረታት ይልቅ ጥቁር ገበያን ያበረታታል::

- ስህተቱ የት ጋ ነው?

- ፖ. ሊ . ሲ!!

(ክቡር ሚኒስትሩ ከአማካሪያቸው ጋር ለዓለም አቀፍ ስብሰባ አሜሪካ ውስጥ ይገኛሉ:: ለሻይ ዕረፍት እንደተወጣ የስብሰባው ተሳታፊ የሆነና አሜሪካ ውስጥ የሚኖር አንድ ኢትዮጵያዊ አብሮ ሻይ ለመጠጣትና ለመተዋወቅ ተቀላቀላቸው)

Page 30: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 30|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

ዲቨንተስ ዊንድ ቴክኖሎጂስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበርየጨረታ ማስታወቂያ

ዲቨንተስ ዊንድ ቴክኖሎጂስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ትንንሽ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን ከጅቡቲ አዲስ አበባ በደረቅ ወደብ በኩል በ6 ባለ 40 ፊት ኮንቴነር ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህም ለቡ ኢንዱስትሪ ዞን ን/ላ/ክ/ከተማ ቀበሌ 15 የቤት ቁጥር አዲስ በሆነው ድርጅታችን አስፈላጊውን የጉምሩክ ፎርሟሊቲዎችን አሟልተው የሚያስገባ ትራንዚተር በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-

1. ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፣

2. የጨረታ ማስከበሪያ እና ያቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ የሚችሉ፣

3. ተጫራቾች አገልግሎቱን ለማቅረብ የሚሰጡትን ዋጋ ከጨረታ ሰነዱ ላይ በተያያዙ የዋጋ ማቅረቢያ ላይ ካሰፈሩ በኋላ የጨረታ ማስከበሪያውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ አያይዞ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ታህሳስ 12/2005 ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ድረስ ን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ለቡ መብራት ኃይል አደባባይ ወደ ቃሊቲ በሚወስደው መንገድ 300 ሜትር ገባ ብሎ በሚገኘው ቢሮአችን ድረስ በመምጣት የጨረታ ሰነዱን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

4. ጨረታው ታህሳስ 15/2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4 ሰዓት ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

5. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0114 19 88 42/43 መደወል ይቻላል፡፡

ዲቨንተስ ዊንድ ቴክኖሎጂስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር

ሀገር መከላከያ ሚኒስቴርየጨረታ ማስታወቂያ

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የመከ/መሠ/ልማት ግንባታ ዘርፍ ለዘርፉ አገልግሎት የሚውሉ፣

ተ.ቁ የንብረቱ ዓይነት መግለጫ

1 የመታወቂያ ፕሪንተር ማሽን DTC-550 ፉርጎ ፕሪንተር With Lamination

2 ላምኔተር የመታወቂያ ካርድ ማሸጊያ ማሽን

3 ዲጂታል ፎቶ ግራፍ ካሜራ (ሳይበርሹት ካሜራ) 12(16)

4 ኤክስተርናል ሀርድ ዲስክ 500 ጂቢ Toshiba or My passport

5 የመታወቂያ ፕሪንተር ማጽጂያ (Clean kit)

6 የካሜራ ማጽጂያ (Clean kit)

7 ሚሞሪስቲክ 1000

8 ላፕቶፕ ኮምፒዩተር ከነ አባሪው ዕቃዎች Care J7Toshiba 6GB RAM 6400HD

9 ዴስክ ቶፕ ኮምፒዩተር ከነ አባሪው ዕቃዎች Del 79 2GRAM 500HDD

ከላይ የተገለጹትን ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋዛብል፡፡

1. በሁሉም ዕቃ ላይ በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣

2. የግብር መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው፣

3. የግዥ መጠን ብር 50, 000.000 /ሃምሳ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፣

4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትን እና ይጠቅመኛል የሚሉትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣

5. የሚገዙትን የዕቃዎች ዓይነት ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፍኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፣

6. የሚገዙ ዕቃዎች ሰነድ ለእያንዳንዱ የማይመለስ ብር 20/ሃያ ብር/ ብቻ በመክፈል ከዘርፍ ዋና ገንዘብ ያዥ ማግኘት ይችላሉ፣

7. ተጫቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢን ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ብር ወይም የዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ 5,000.00 /አምስት ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲ.ፒ.ኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ፣ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፣

8. ለማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሂሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋናውንና ቅጂ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ለግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን በተዘጋጀው ሳጥን

ዘወትር በስራ ሰዓት ይህ ጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከታህሳስ 04/2005 ዓ.ም. እስከ 4፡00 ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ እስከ ጥር 04/2005 ዓ.ም. በ4፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡

9. ከላይ የተገለጹን ዕቃዎች አጠቃለው ማቅረብ የሚችሉ፣ ላቀረቧቸው ዕቃዎች በቂ ዋስትና እና የጥገና አገልግሎት በተጨማሪ በዕቃዎቹ ለሚገለጉ ሙያተኞች ስለ እቃዎች አጠቃቀም ነጻ ስልጠና የሚሰጡ እና ዕቃዎቹን ገጣጥመው መጀመራቸውን አረጋግጠው ማስረከብ የሚችሉ፣

10. በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ ተጫራቾች በመመሪያው መሰረት ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡

11. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

12. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0911-152211 ወይም 0911-043690 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

አድራሻ፡ ወሎ ሠፈር ብራና ማተሚያ ውስጥ የመከላከያ መሠረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ ብለው ይጠይቁ ወይም ይደውሉ፡፡

የመከላከያ መሠረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን

ምሥራቅ ዱቄትና ዳቦ ፋብሪካ

MISRAK FLOUR & BREAD FACTORY( 011-465 32 55 465 18 16

ቴሌ ፋክስ 00 251-11-465 53 44

416 14 67

465 37 95

ተ.ቁ ክፍት የሥራ መደብ

ብዛት ተፈላጊ ችሎታ የሥራ ልምድ ደመወዝ

1 ሲኒየር ኮስት አካውንታንት

1 በአካውንቲንግ ቢ.ኤ.ዲግሪ እና

በአካውንቲንግ ኮሌጅ ዲፕሎማ (10+3) የፒችትሪ ዕውቀት ያለውና በምግብ

ፋብሪካ የሠራ ቢሆን ይመረጣል፣

በሙያው 4 ዓመት የሥራ ልምድ ያለው ወይም

በሙያው 6 ዓመት የሥራ ልምድ

በስምምነት

2 ኮስት አካውንታንት 1 በአካውንቲንግ ቢ.ኤ ዲግሪ እና

በአካውንቲንግ ኮሌጅ ዲፕሎማ (10+3) የፒችትሪ ዕውቀት ያለውና በምግብ

ፋብሪካ የሠራ ቢሆን ይመረጣል፣

በሙያው 2 ዓመት የሥራ ልምድ ያለው ወይም

በሙያው 6 ዓመት የሥራ ልምድ

በስምምነት

3 ሽያጭ ሠራተኛ 5 በማርኬቲንግ /በሴልስ/ በአካውንቲንግ ኮሌጅ ዲፕሎማ (10+3)

ወይም ሙያና ቴክኒክ (10+2) ዲፕሎማ

ቢቻል ከ1 ዓመት በላይ የሥራ ልምድ ያለው

በስምምነት

4 ኬሚስት 1 ቢ.ኤስ.ሲ ዲግሪ ወይም ኮሌጅ ዲፕሎማ

(10+3)

በኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ 2 ዓመት

ወይም በኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ 6 ዓመት

የሠራ

በስምምነት

አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ማስረጃችሁን በመያዝ ሠራተኛ ማስተዳደሪያና ሥልጠና ክፍል ቢሮ ቁጥር 11 በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

አድራሻ፡- ጐተራ ትራፊክ ማሳለጫ አጠገብ ቶታል ዴፖ በስተጀርባ

ምሥራቅ ዱቄትና ዳቦ ፋብሪካ

ስልክ ቁጥር፡- 0114-651816

Page 31: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 31 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

Tekleberhan Ambaye Construction P.L.C.(TACON)

Notice of Invitation for Expression of Interest (EoI)

for Organizational Change Facilitation Technical Assistance

Ref. No: TACON/NIEI/MC/03/2012

Company OverviewTekleberhan Ambaye Construction P.L.C. (TACON) is one of the leading Ethiopian class 1 construction companies that has been in business since 1993. TACON is privileged to undertake numerous complex building projects throughout the country while its business empire has further extended to neighboring Somaliland Republic. Besides striving to maintain industry leadership position, the commitment of management for continual improvement coupled with the company’s pioneering the local industry for ISO certification allows TACON to pick up the prestigious national award of “Best Contractor of Year 2012” bestowed by the Federal Democratic Republic of Ethiopia (FDRE) Government Ministry of Urban Development and Construction.

Project BackgroundSince 2010 TACON has been engaged in a change process. This transformation is largely due to the growing concern to successfully facing the challenges that the globally competitive environment poses on the construction industry in particular. Among others, management has recently formulated a strategic plan that aims at excelling in providing differentiated infrastructure development solutions thereby further entrenching the company’s position towards a pacemaker transnational construction contractor.The Office of the Senior Deputy General Manager (OSDGM) of TACON is charged with coordinating the organizational change efforts and has embarked on taking the action steps required to sustainably managing the transformation process. To this end, the OSDGM has assigned task force members to dealing with the day-to-day management of change operations despite its firm belief for that the participation and effective use of an independent consultant that can bring the best balance between institutional knowhow and creative fresh thinking.

The AssignmentThe OSDGM now solicits sealed bids from eligible firms with demonstrated expertise in facilitation of change management, business process re-engineering (BPR), organizational development (OD) or strategy formulation, to express their interest to technically assist in the implementation of the intended transformation project. The expertise of an independent consultant or association of consultancy firms is mainly sought to provide a professional and objective assessment on organizational readiness for change; assisting in developing mechanisms and tools during the course of process mapping and rationalizing as well as providing on-going technical support during the implementation phase to ensure successful transition and the outcomes envisaged from the project are realized.

Bidding ProceduresInterested local and international consultants may obtain further information and inspect the Terms of Reference (TOR) that highlights the objective, scope, deliverables, evaluation criteria and etc. of the assignment at the office of the Executive Secretary of the SDGM on the 1st floor of TACON’s new Head Quarters premises, close to the CMC - Meri Square adjacent to the compound of the School of Tomorrow. Alternatively, the document can be sought after from Room No. 16 (the 2nd floor) of Yayeh Yirad Building on the Ethio - China Avenue behind Wongelawit Building.A complete set of bidding documents may be purchased effective December 14, 2012 by interested consultants upon submission of a written application and payment of a non-refundable fee of Ethiopian Birr (ETB) 200 (Two Hundred) or its equivalent in easily convertible currency transferred to or deposited on Account No. 0171849702800 labeled “Tekleberhan Ambaye Construction P.L.C.” maintained at the Kera Branch of the Commercial Bank of Ethiopia (CBE). The SWIFT CODE of the bank account is CBETETAA.A pre-bid meeting is scheduled to be held at 09:30 am (local time) on Thursday 27th December, 2012 at the Executive Meeting Hall of TACON in its CMC based Head Quarters building. The original and a copy of the Technical Proposal and Financial Offer should be submitted in sealed envelopes or delivered by registered post marked “Expression of Interest for Organizational Change Facilitation Technical Assistance” along with copies of qualification and other relevant documents not later than Monday 21st January, 2012 at 12:00 am (local time). The bid must be accompanied by a bid security of ETB 10,000 (Ten Thousand) Ethiopian Birr or its equivalent in the form of cash, a certified check or bank payment order, bank draft, letter of credit or an unconditional bank guarantee in any freely convertible currency issued by a locally acceptable bank. The bidders’ offers shall be valid for a period of 45 days after bid opening while the bid security is required to stay valid for additional 15 days.Expression of Interest (EoI) responses that are not received by the given deadline will be returned unopened. The Technical Proposal will be opened in the presence of bidders’ representative who choose to attend, on 21st January, 2012 at 02:30 pm (local time) in the Meeting Hall of TACON. Selection of the successful bidder shall be made by the highest points total of the evaluation results of both the Technical and Financial proposals. Tekleberhan Ambaye Construction P.L.C. (TACON) reserves the right to accept or reject any or all applications for EoI without the need for providing justifications whatsoever.

Contact and Submission Detail Office of the Senior Deputy General Manager (OSDGM) Tel: +(251) 118-964-810/17Tekleberhan Ambaye Construction P.L.C. (TACON) Mobile: +(251) 911-464-552CMC - Meri Square Fax: +(251) 114-426-146P.O. Box 8291 Addis Ababa - Ethiopia e-mail: [email protected] e-mail: [email protected]

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያቃኘው ሻለቃ ኃ.የተ.የግ.ማ. ለማርስ ሚስማር ፋብሪካ የሚሆኑ ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

ተ.ቁ የሥራ መደብ መጠሪያ

ተፈላጊ ችሎታ ብዛት የስራ ቦታ

1 የፋብሪካ ስራ

አስኪያጅ

በማኔጅመንት ወይም በአካውንቲንግ ወይም በሜካኒካል ኢንጅነሪንግ

በመጀመሪያዲግሪ የተመረቀ/ችና በፋብሪካ ውስጥ

በኃላፊነት ሁለት ዓመት የሰራ/ች፣ በቂ የእንግሊዝኛ

እውቀት ያለው/ላት

1 አለም ገና ልዩ ስሙ ወለቴ

2 ፀሐፊ በሴክሬቴሪያል ሳይንስ እና ኦፊስ ማኔጅመንት በዲፕሎማ የተመረቀች እና መሰረታዊ የአካውንቲንግ እውቀት ያላት

2

ከዚህ በላይ የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች CV፣ የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃችሁን በማያያዝ እስከ ታህሳስ 10 2005 ዓ.ም

[email protected] መላክ

ወይም

ቦሌ መንገድ፣ ሜጋ ህንፃ፣ 1ኛ ፎቅ ቢ.ቁ 116 መስጠት ትችላላችሁ፡፡

VACANCY ANNOUNCEMENT

Wadi El Sundus Petroleum Co. Ltd. Ethiopian Branch is looking for qualified candidates for the following position.

Position-SecretaryEducational Qualification – BA degree in Secretarial Science and Office Management or any related field from a recognized college.

Work Experience – Two years and above. Language requirement- Fluency in spoken and written EnglishPlace of Work – Addis Ababa Salary-Negotiable

Interested applicants can send or submit in person their application along with their CV within seven consecutive days from the date of this announcement to:

Wadi El Sundus Petroleum Co. Ltd. Eth. BranchBole Medhanialem Church Area

Gulf Aziz Building, 5th Floor, Office No. 501/BTelephone 0116 18 02 18, Fax 0116 18 02 19

ማስታወቂያ

Page 32: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 32|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

..

ማስታወቂያ

Page 33: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 33 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ፎቶ ዜና

ሠላም ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ፌስቲቫል በቅዳሜ ቆይታው

ፎቶ በሪፖርተር/ናሆም ተስፋዬ

ስቱዋርት ሲኮማ (ሞዛምቢክ)

ሱሱና ማህር (ስዊድን /ሴኔጋል/)

ማህሙድ አህመድ (ኢትዮጵያ)

ሳክሲፎኒስት ያሬድ ተፈራ

ተመልካቾች

ተመልካቾች

Page 34: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 34|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

ዓለም አቀፍ

ግብፃውያንን ለሁለት የከፈለው ረቂቅ ሕገ መንግሥትየቀድሞ ፕሬዚዳንታቸውን ሆስኒ ሙባረክን

ከሥልጣን ለማውረድ በአብዛኛው አንድነትን ያሳዩት ግብፃውያን፣ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ወደ ፕሬዚዳንትነት ያመጧቸው መሐመድ ሙርሲ በቅርቡ በፈጸሙት የሥልጣን ሽሚያና የሕገ መንግሥት ረቂቅ ምክንያት ለሁለት ተከፈሉ::

በታህሳስ አጋማሽ ላይ ሕዝበ ውሳኔ ይሰጥበታል የተባለውና ለፕሬዚዳንት ሙርሲ የፍትሕ አካሉን ድርሻ ጨምሮ ቁልፍ ሥልጣን የሚያጐናፅፈው ረቂቅ ሕገ መንግሥት ለግብፃውያኑ መከፋፈል መንስዔ ሆኗል::

የፕሬዚዳንት ሙርሲ ፓርቲ የሆነው የሙስሊም ብራዘርሁድ ደጋፊዎች ረቂቅ ሕገ መንግሥቱን ሲደግፉ፣ የቀድሞው የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ሞሐመድ አልባራዲን ጨምሮ ታላላቅ የግብፅ ፖለቲከኞችና ምሁራን ተቃውመውታል::

ወሳኝ ሥልጣኖችን ጠራርጐ ለፕሬዚዳንት ሙርሲ የሚያጐናጽፈው ረቂቅ ሕገ መንግሥት ለግብፃውያኑ መጋጨትና መከፋፈል ምክንያት ሆነ እንጂ ሰላምን አላመጣም::

ለአብዛኛው ግብፃውያንንም በካይሮ ቤተ መንግሥትና በታህሪር አደባባይ የተቃውሞ ሠልፍ እንዲወጡ ምክንያት ሆኗል:: ተቃዋሚዎችም ለታህሳስ አጋማሽ የታቀደው ሪፈረንደም እንዳይካሄድ ቅስቀሳ እያደረጉ ነው::

ግብፅ በፕሬዚዳንት ሙርሲ ሳቢያ ውጥረት ውስጥ በመግባቷ ምክንያት ችግሩን ለማርገብ ፕሬዚዳንቱ የውይይት መድረክ በቤተ መንግሥታቸው ያዘጋጁት ባሳለፍነው ሳምንት ማብቂያ ላይ ነበር:: በውይይቱ ላይ ከፍተኛ የፖለቲካ ተንታኞችና ተቃዋሚዎች ተገኝተዋል::

ዥንዋ እንደዘገበው፣ ፕሬዚዳንት ሙርሲ

ከተቃዋሚዎች ጋር ለዘጠኝ ሰዓታት ያህል ውይይት ካደረጉ በኋላ የቀድሞው ሕገ መንግሥት አዋጅ ሙሉ ለሙሉ ተሰርዞ አዲስ ተዘጋጅቷል:: ሆኖም በአዲሱ ረቂቅ ሕገ መንግሥት ላይ መሠረታዊ የሆኑ ጉዳዮች አልተቀየሩም::

ፕሬዚዳንት ሙርሲ የሕገ መንግሥት ማርቀቂያ አዋጁን ለመሰረዝ የተገደዱትም በስብሰባው የተገኙ ፖለቲከኞች ጫና ከፈጠሩባቸው በኋላ ነው ተብሏል::

ፕሬዚዳንት ሙርሲ ሥልጣን ጠራርጐ የሚያጐናጽፋቸውን ረቂቅ ሕገ መንግሥት ለሪፈረንደም ለማቅረብ የወጣውን አዋጅ አሻሽያለሁ ቢሉም፣ ተቃዋሚዎቻቸው ግን ሪፈረንደሙ እንዳይካሄድና እንዲራዘም አሁንም እየወተወቱና ተቃውሟቸውንም እየገለጹ ናቸው:: በፕሬዚዳንት ሙርሲ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች መካከልም ግጭቶች እያየሉ ነው::

ቢቢሲ እንደዘገበው፣ የግብፃውያኑ ግጭት

አገሪቱን ለሁለት ከፍሏታል:: ይህ ደግሞ ወደከፋ ግጭት እንዳያመራ ሥጋት ፈጥሯል:: ግብፃውያን ሙስሊሞች፣ ኮፕቶች፣ ሊበራሎችና ሌሎች በታህሪር አደባባይ በአንድነት ሆነው የሆስኒ ሙባረክን የ30 ዓመታት አገዛዝ እንዳልገረሰሱ ሁላ፣ ዛሬ ግን ለሁለት ተካፍለው ተፋጠዋል:: ግብፅ በውስጥ ፖለቲካዋ ምክንያት የተፈጠረው ልዩነቷ በጊዜ መላ ካልተባለ አደገኛ ችግር ይገጥማታል እየተባለም ነው::

በደጋፊዎቻቸውና በተቃዋሚዎቻቸው መካከል የተፈጠረው ግጭት ያላማራቸው ፕሬዚዳንት ሙርሲ ለአገሪቱ መከላከያ ተጨማሪ ሥልጣን መስጠታቸው ተዘግቧል:: ቢቢሲ እንደዘገበው ከሆነ፣ ሕዝብንና አገርን እንዲጠብቅ ኃላፊነት የተሰጠው የመከላከያ ክፍሉ የፖሊስን ሥልጣን በመጐናፀፍ ለተቃውሞ የሚመጡትን እንዲያስር ትዕዛዝ ተሰጥቶታል:: ይህ ደግሞ የተቃዋሚዎችን ተቃውሞ አጋግሎታል::

ለፕሬዚዳንት ሙርሲ ከቀድሞው ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ የበለጠ ሥልጣን ያጐናፅፋል የተባለውን ረቂቅ ሕገ መንግሥት በመቃወም ወደ ጐዳና ከወጡ ተቃዋሚዎች ከ600 በላይ ጉዳት ሲደርስባቸው ሰባት መሞታቸው ተሰምቷል::

ፕሬዚዳንት ሙርሲ ምንም እንኳ በጠባብ የድምፅ ልዩነት ድኅረ ሙባረክ ምርጫን ቢያሸንፉም፣ የሚወክሉት የሙስሊም ብራዘርውድ ድርጅት አክራሪ እስልምናን ለማስፋፋት ጥረት እያደረገ ነው በመባል እየተተቸ ነው:: ይህንን እንቅስቃሴ ለማስቆም ተነስተናል ያሉት የግብፅ ተቃዋሚዎች አንድ የጋራ ግንባር በመፍጠር ሙስሊም ብራዘርሁድንና ፕሬዚዳንት ሙርሲን እንቅልፍ ለመንሳት ተነስተዋል:: የፕሬዚዳንቱ ደጋፊዎች ይህንን እንቅስቃሴ ለማስቆም በንቃት መንቀሳቀስ ጀምረዋል:: ግብፅ ይህ ዓይነቱ አጣብቂኝ ውስጥ ገብታ ታህሪር አደባባይ ላይ የተቀጣጠለው አብዮት ወዴት እንደሚጓዝ ግራ በመጋባት ስሜት እያየችው ነው::

በአሁኑ የግብፃውያን መከፋፈል ታህሪር አደባባይ ላይ በአንድነት ያመጡት አብዮት ወዴት ያመራ ይሆን የሚል ጥያቄ እያስነሳ ነው

ፎቶ ዜና

ኅዳር 29 ቀን 2005 ዓ.ም. በባህር ዳር ከተማ ሰባተኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ሲከበር የተለያዩ ብሔረሰቦች ሙዚቃዎቻቸውን በባህር ዳር ስታዲየም አቅርበው ነበር ፎቶ በመስፍን ሰለሞን

Page 35: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 35 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

የት?‹‹ሰው መሆን ይሻላል››አዲሱ የግጥም መድበል

‹‹ሰው መሆን ይሻላል›› በሚል ርእስ የ52 ግጥሞቹን መድበል ያሳተመውና መሰንበቻውን ለንባብ ያበቃው አረጋ ኃይለ ሚካኤል ነው::

ገጣሚው በመግቢያው እንዳለው መድበሉ የሚያጠነጥነው ሰው በመሆን ዙሪያ ነው:: ሰው የመሆንን ሒደትና ሁነቶች፣ ሰው የመሆንን ውጤትና አንድምታ የት ድረስ ሊሆን እንደሚችል ለማየት ይሞከራል:: የመድበሉ ዋጋ 18 ብር መሆኑ ታውቋል::

‹‹ሕያው ጥበብ›› የዳንስ ፊልም እሑድ ይመረቃል

ሔልጌት ኢንተርቴይመንት እና ዲጄ ዊሊ ኢንተርቴይመንት ያዘጋጁት ‹‹ሕያው ጥበብ›› የተሰኘ የዳንስ ዲቪዲ እሑድ ታኅሣሥ 7 ቀን 2005 ዓ.ም. በ10 ሰዓት በሐርመኒ ሆቴል ያስመርቃሉ::

ፊልሙ ከተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ በመነሣት አስተማሪ የሆኑ አጫጭር ታሪኮችን የሚፈጥረው ያለምንም ቃለ ተውኔት (ዲያሎግ) በዳንስ ኬሮግራፊ ብቻ ነው:: በአስቂኝ ድርጊቶች የተሞላው ፊልሙ፣ ኅብረተሰቡ ሊገባው በሚችል መልኩ የተሠራና በዲቪዲ እና በቪሲዲ የሚሠራጭ መሆኑ ሔልጌት አስታውቋል::

በስሜት የተሞላ ቀን

በጥበበሥላሴ ጥጋቡ

በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ አሻራቸውን መጣል ከቻሉ ስመ ጥሩ ዘፋኞች ውስጥ አንዱ ማህሙድ አህመድ ነው:: በኢትዮጵያውያን ዘንድ ተወዳጅነትን፣ ተደናቂነትን፣ ተፈቃሪነትን ማትረፍ የቻለ ፈርጥ እንደሆነ ብዙዎች ያምናሉ:: ሙሉ ሕይወቱን በሙዚቃ ያሳለፈው ማህሙድ በሙዚቃው ይተነፍሳል፣ ይናገራል፣ ሰውን ያዝናናል:: ከአርባ ዓመታት በላይ በቆየውም የሙዚቃ ሕይወቱ የተለያዩ ትውልድን በሙዚቃው አንድ ላይ ማምጣት የቻለ ትልቅ አርቲስት ነው:: በተለያዩ ኮንሠርቶች በሚዘፍንበትም ወቅት በተለያዩ ዕድሜ ክልል የሚገኙ ሰዎች ብሔራዊ መዝሙር በሚመስል መልኩ አብረውት በመዝፈንም በዘፈኑ አንድነትን ያሳያሉ::

ማህሙድ የዝና ጣራ ላይ መድረስ ችሏል:: በሕዝቡ ዘንድ ከመወደዱና ከመፈቀሩ በተጨማሪ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይም ዝናው ናኝቷል:: የሰዎችን ልብ ከማሸነፉ በተጨማሪ ከኮንሠርቱ በፊት ቲኬቶቹ ተሸጦ የሚያልቅበት አጋጣሚም ተደጋጋሚም ነው:: የተለያዩ ሽልማቶችንም ለማሸነፍም ችሏል:: ከእነዚህም ውስጥ አንዱ የቢቢሲ ወርልድ ሚዩዚክ አዋርድ አንዱና ዋነኛው ነው:: ምንም እንኳን ይሔን ያህል የጣራ ዝና ላይ ቢሆንም ትሁት፣ ሰዎችን የሚያከብርና በቀላሉም የሚግባባ ሰው ነው::

ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ነበር የሰላም ዓለም አቀፍ ሙዚቃ ፌስቲቫል አካል ሆኖ ከያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጋር ሙዚቃ ሕይወቱን ያካፈለው:: አዳራሹ በተማሪዎች ተሞልቶ የነበረ ሲሆን ለብዙዎች ማህሙድን ማየት ትልቅ ነገር ነው:: በተለይም በአካል ተገኝቶ ከእነርሱ ጋር ማውራቱ እንደ ዕድልም ነው ያዩት:: በሚያስደንቅ ሁኔታ ግን ማህሙድ በስሜት ተሞልቶ ከተማሪዎቹ በላይ ያለቀሰበት ሁኔታ ታይቷል:: በሳግ በተቆራረጠ ድምፅም እዚህ ቦታ ላይ መገኘቱ ለእሱ ልዩ እንደሆነም ተናግሯል::

‹‹ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ከተማሪዎች ጋር ስለሙዚቃ ሕይወቴ ሳወራ፤ ዛሬ ብሞትም ምንም አይመስለኝም:: በጣም ዕድለኛ ነኝ:: እግዚአብሔርም በሕይወት ያቆየኝ ለዚህ ይመስለኛል፤›› ብሏል::

ማህሙድ ከልጅነቱ ጀምሮ ያጋጠመውን ውጣ ውረድ በማስታወስ አሁን ያለበትን ደረጃም እግዚአብሔርን በማመስገን ተናግሯል::

የተወለደው በ1933 ዓ.ም. አዲስ አበባ በአሜሪካን ግቢ አካባቢ ነው:: ሥራንም ሆነ ሕይወትን በራሱ መጋፈጥ የጀመረው ገና በሕፃንነቱ ነው:: አባቱ በሚሠራበት ግሪክ ክለብ አብሮ በመሔድ ቅርጫት ኳስና የቴኒስ ሜዳዎቹ ላይ ይሠራም ነበር:: በስድስት ዓመቱም ሊስትሮ ሆኖ መሥራት ጀመረ:: በትምህርት ቤት ቆይታው ብዙ ጐበዝ እንዳልነበር ፈገግ ብሎ የሚያወራው ማህሙድ ቤተሰቦቹንና ራሱን መርዳት እንዳለበትም የተረዳው ገና በሕፃንነቱ ነው::

የሙዚቃ ሕይወቱ ሀ ብሎ የተጀመረው አንድ ክለብ ውስጥ ሳንድዊች እንዲያቀርብ በተቀጠረበት ጊዜ ነው:: እንደ አጋጣሚም ሆኖ በዚያው ክለብ ውስጥ ጥላሁን ገሠሠ ይዘፍንበት የነበረ ቦታ ነበር::

በአንድ አጋጣሚም ሁሉም ድምፃውያን ወደ ድሬዳዋ ሔደው ሙዚቀኞቹ ያለ ድምፃዊ እየተለማመዱ ነበር:: የተፈራ ካሣን ‹‹አልጠላሽም ከቶ››ን የተዘራን ‹‹ይሔም አለ ለካ››ንና የጥላሁን ዘፈን እየተለማመዱ ነበር:: በድምፅ መዝፈን እንደሚፈልግም ጠየቃቸው::

‹‹በጣም ቀጭን ነበርኩ እናም ‘ትችያለሽ? ወይ›› ብለው ጠየቁኝ፣ እናም እሞክራለሁ አልኩ›› በማለት ማህሙድ ይናገራል:: ‹‹አልጠላሽም ከቶ›› የሚለውን ዘፈን በሚዘፍንበት ሰዓት የኮንጐ ዘማቾች በቦታው ነበሩ እናም አስደነቃቸው:: እንደገናም እንዲዘፍን ተጠየቀ:: የክለቡ ባለቤት በቦታው የነበረ ሲሆን አድናቆት በተሞላ ድምፅም ‹‹የአላህ ያለ መዝፈን ትችላለህ!›› እንዳለው ማህሙድ ያስታውሳል በዚህም አጋጣሚ ከአስተናጋጅነት ወደ ዘፋኝነት ተቀየረ:: የቤቱ ባለቤትም ሙሉ ልብስ ገዛለት::

ጥላሁንና ሌሎቹ ዘፋኞች በተመለሱበት ወቅት የእሱ መዝፈን በጣም ነው ያስገረማቸው፤ የግጥም ደብተርም ሰጡት:: መዝፈን በጀመረበት ወቅት የተለያዩ ዘፋኞችን ሙዚቃ በመዝፈን ነበር:: በዚህም ክለብ ነበር ‹‹አላወቅሽልኝም›› የሚለው የመጀመሪያው ዘፈኑ የሆነው ግጥም የተሰጠው:: ክብር ዘበኛ መቀጠር ፍላጐቱ የነበረ ሲሆን መጀመሪያ ግን ፖሊስ ኦርኬስትራና ምድር ጦር ለመቀጠር ጠየቀ:: በተለያዩ ምክንያቶችም እንደማይቀጥሩት ነገሩት:: መቶ አለቃ ግርማ ሐድጉም (በኋላ ሻለቃ) ክብር ዘበኛ መቀጠር ይፈልግ እንደሆነ ጠየቁት፣ እሱም ተስማማ ከመቀጠሩ በፊት ግን በሕዝብ ፊት ዘፍኖ ማለፍ ነበረበት:: የዚያን ጊዜ የነበረውን እያንዳንዷን ጥቃቅን ነገር በጥልቅ ያስታውሳል፤ የታምራት ሞላን ‹‹ተስፋ አትቁረጪ›› እንዲሁም ‹‹አላወቅሺልኝም››ን ሲዘፍን የተመልካቹ መልስ ለየት ያለ ነበር::

‹‹የኤልቪስ ፕሪስሊን ዳንስም እየደነስኩ ነበር፣ እናም የተመልካቹ መልስ የማይታመን ነበር፤›› በማለት ማህሙድ ይገልጻል::

መቶ አለቃ ግርማም ወታደር ሆኖ እንዳይቀጠር መከሩት፣ የክብር ዘበኛ ሰዎችም በወታደርነትና ሙዚቀኝነት 120 ብር እንክፈልህ ብለው ጠየቁት:: እሱ ግን ባለመስማማቱም በሙዚቀኝነት ብቻ በ1955 ዓ.ም. አካባቢ ተቀጠረ:: ለአሥራ አንድ ዓመታትም ያህልም በዚህ ቦታ ሠርቷል::

‹‹ለዚህ ያበቃኝ፣ የማውቀውን ነገር ሁሉ ያስተማረኝ ለእኔ ወንድሜ ጥላሁን ገሠሠ ነው:: ሌሎችም ሙዚቀኞች እንዲሁ በእኔ ላይ አሻራ ጥለዋል፤›› ይላል ማህሙድ::

በዚያን ወቅት ሙዚቀኞች አንድ ላይ ይሰባሰቡበት የነበሩ ብዙ አጋጣሚዎች ነበሩ:: ከእነዚህም ውስጥ ክብር ዘበኛ ይሠራ በነበረበት ወቅት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ይደረግ የነበረው የሙዚቀኞች ውድድር አንዱ ነው::

የተለያዩ ባንዶች እንደ ምድር ጦር፣ ክብር ዘበኛና የፖሊስ ኦርኬስትራ ባንዶች ከድምፃውያኖቻቸው ጋር ይመጣሉ:: እያንዳንዱም ድምፃዊ አንድ ወይም ሁለት ዘፈን ይዘፍናል:: ይሔም ለሙዚቀኞች ጥሩ አጋጣሚ እንደነበር ይናገራል:: ከአሥራ አንድ ዓመታት ቆይታም በኋላ በተለያዩ ክለቦች መሥራት ጀመረ:: ለዚህም ምክንያቱ የነበረው ያገኘው የነበረው 60 ብር

አምስት እህቶቹና ወንድሞቹ በአጠቃላይ ቤተሰቦቹን መደገፍ አልቻለም::

በወቅቱ አባቱ ሥራ ያልነበራቸው ሲሆን እናቱ ብቻ ነበረች የምትሠራው፤ መጨረሻ ላይ ከክብር ዘበኛ በለቀቀበት ወቅት ደመወዙ 250 ብር ደርሶ ነበር፤ ከዚያም ከአይቤክስ ባንድ ጋር ተጠቃልሎ ራስ ሆቴል ተቀጥሮ መሥራት ጀመረ::

በሙዚቃ ሕይወቱ ውስጥ ብዙ ውጣ ውረዶችን እንዳሳለፈ የሚናገረው ማህሙድ ዘመኑ ለሙዚቀኞችም ሆነ ለሙዚቃ ዕድገት የተመቻቸ እንደሆነ ይገልጻል:: እንደሚናገረው ከሆነ ይሔ ዕድገትም የተገኘውና እዚህ መድረስ የተቻለው በዱሮ ሙዚቀኞች መስዋዕትነት ነው::

‹‹እነዚህ ሙዚቀኞች አሻራቸውን ጥለው ማለፍ ችለዋል፤›› የሚለው ማህሙድ በዚያን ጊዜ የነበሩት ሙዚቀኞች ምንም እንኳን ችሎታው ቢኖራቸውም የሙዚቃ ትምህርት ቤት አልሔዱም:: የዚያን ጊዜውንም በማስታወስ ለሙዚቀኞች እንዴት ከባድ እንደነበር ይናገራል:: ሙያውም እንዴት ይናቅ እንደነበርም ያስታውሳል::

በ1963 ከአይቤክስ ባንድ ጋር ራስ ሆቴል በሚሠራበት ወቅት ‹‹ኩሉን ማን ኳለሽ››፣ ‹‹አምባሰል››፣ ‹‹ችቦ አይሞላም ወገቧ›› እና ‹‹አልማዝ ምን ዕዳ ነው›› የመሳሰሉ ዘፈኖችን ይዘፍን ነበር:: እነዚህ ዘፈኖች ከአንዳንድ ወገኖች ከፍተኛ ትችትም አጋጠመው:: የዱሮ ዘፈኖችን በአዲስ መልክ ትጫወታለህ ለማለት አንድ ጋዜጠኛ ‹‹ፍራሽ አዳሽ›› ብሎ የጠራውን አጋጣሚም አሁንም አይረሳውም::

‹‹አላዘንኩም:: የዱሮ ዘፈኖችን አዲስ ሕይወት በመስጠት ዘፍኛለሁ:: ፍራሽም እንደ አዲስ ሲታደስ ይተኛበታል›› ይላል:: ማህሙድ ከዚህም በተጨማሪ ‹‹ዓባይ ማዶ››፣ ‹‹ደኑን ጥሰሽ›› እና ‹‹የት ነበርሽ›› የሚሉት ዘፈኖቹም የተለየ ርዕዮተ ዓለም ያስተላልፋሉ በሚልም ተወቅሶ ነበር::

የማህሙድ ዓለም አቀፍ ዕውቅና የመጣው ፍራንሲስ ፋልሴቶ ኢትዮጲክስ የሚለውን የሙዚቃ ስብስብ ካወጣ በኋላ ሲሆን ማህሙድም ውለታውን የረሳ አይመስልም::

ፋልሴቶ ፈረንሣዊ ፕሮሞተር ሲሆን የማህሙድን ‹‹መላ መላ›› የሚለውን ዘፈን ሬዲዮ ላይ ሰምቶ አብረን እንሥራ ብሎ ጠየቀው፣ ማህሙድ መጀመሪያ ላይ ተጠራጥሮ እንደነበር ያስታውሳል::

እየተደራደሩ ባሉበት በ1960ዎቹ አካባቢ ማህሙድ ወደ ፈረንሣይ አቅንቶ ሙላቱ አስታጥቄ ጋር አብሮ ዘፍኗል:: በዚያችው ከተማም ማይክል ጃክሰን በዚያው ምሽት ዘፍኗል:: ከተመለሰም በኋላ ነው ኢትዮጲክስ የወጣው::

በዚሁ መድረክ ላይ አዲስ እየሠራው ያለውን ‹‹አብራኝ ናት›› ስለሚለው ዘፈኑም ተናግሯል:: አዳራሽ ውስጥ እየጠቆመ ምን ያህል እንደሚያፈቅራትም ተናግሯል:: ‹‹አብራኝ ናት ከልጅነት እስከ ዕውቀት አብራኝ ናት:: እዚሁ አለች በመንፈስም በሥራዎቼም ውስጥ አብራኝ ናት:: እዚህ ለመድረሴም ምክንያት እሷ ናት:: ትመክረኛለች፤ ከዓመታት በፊት ‹‹አልማዝ አልማዝዬ›› ብዬ ዘፍኘላታለሁ፤ አሁን ደግሞ ‹‹አብራኝ ናት ብዬ›› እዘፍንላታለሁ፤›› ብሏል፤ ማህሙድ::

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/ናሆ

ም ተ

ስፋዬ

Page 36: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 36|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

ማስታ

ወቂያ

ኑሮ

ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር

ክፍት የሥራ ቦታ

ተ.ቁ.የሥራ መደብ መጠሪያ

የት/ደረጃ/ዓይነት የሥራ ልምድ ብዛት የሥራ ቦታ ደመወዝ የቅጥር

ሁኔታ

1ፕላኒንግና ቢዝነስ ቨሎፕመንት

ከታወቀ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም በኢኮኖሚክስ በኤም.ኤ ወይም በቢ.ኤ.ዲግሪ የተመረቀ/ች

በኤም.ኤ.ዲግሪ ቢያንስ 5 ዓመትበቢ.ኤ.ዲግሪ ቢያንስ 7 ዓመት የሥራ ልምድ ያለው/ት

1 አዲስ አበባ በስምምነት በቋሚነት

ከዚህ በላይ የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች የትምህርትና

የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን ከማመልከቻ ጋር

በማያያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አሥር)

የሥራ ቀናት ውስጥ በዋናው መ/ቤት 3ኛ ፎቅ የሰው ኃይል አስተዳደር

ዋና ክፍል ቢሮ ቁጥር 303 በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን

እንገልጻለን፡፡

አድራሻ፡-

ከመገናኛ አደባባይ ወደ ጉርድ ሾላ በሚወስደው መንገድ በማዕድንና

ኢነርጂ ሚኒስቴር ጽ/ቤት አጠገብ ዳሚናሮፍ ሕንጻ 3ኛ ፎቅ የቢሮ

ቁጥር 303 ነው

ስልክ፡- 0116477658

Call for Consultancy Service Documentation of Project Best Practices

Health Limited, a British International NGO, globally trading as Health Poverty Action (HPA), implements various health projects in Ethiopia. The Ethiopia Country Office invites legally registered firms and/or professionals to conduct documentation of Best Practices on:

1. Mobile HIV Voluntary Counseling and Testing (VCT) Services, 2. The Role of Community Conversation in addressing FGM and MCH

issues, and 3. The Role of Project Steering Committee in Project Governance

The best practices documentation will be done under Health Limited’s “Improving the Sexual and Reproductive Health of Pastoralist Communities in Bale Lowlands” project being implemented in Bale Zone of Oromia Regional State, Rayitu and Sawena Woredas, in partnership with Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus – Development And social Services Commission (EECMY-DASSC) and the regional and woreda level government offices. Interested and capable consultancy firms may collect the Terms of Reference (ToR) and submit their technical and financial proposals to Health Limited office located at the address below within 10 calendar days of this announcement. The country office reserves the right to cancel the bid fully or partially.Health Limited, Ethiopia Office, near Axum Hotel on Haile Gebresilassie Street, M&M Building, 3rd Floor, Room No. 303, Yeka Sub-city, Addis Ababa. P.O. Box- 102166 A.A

Telephone number: 0116 612509

በሔኖክ ረታ

ከረር ብላ በወጣችው የረፋዷ ፀሐይ በቆሼ አካባቢ ውር ውር የሚሉትን ሰዎች፣ ውሾችና የሰማይ አሞሮችን ከዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው አልገደበቻቸውም:: ከዋናው የቀለበት መንገድ ማዶ ሆኖ ቆሼን ለሚመለከተው ሁሉ እንኳንስ በዛ ጠራራ ፀሐይ በምሽት ጥላ እንኳን በአጠገቡ ለመቆም አይደለም ለማለፉ የሚሰነፍጠው ባዕድ ሽታ ብቻ ሳይሆን በዓይን የሚታየው የቆሻሻ ክምር ይሰቀጥጣል:: ከቆሼ ባሻገር ካሁን አሁን ደረሰ በሚል ጉጉት ተዘጋጅተው የሚጠብቁ ወጣቶች አሉ:: ሰፋ ያለ ደረቱና ፈርጠም ያሉት ክንዶቹን ባደፈ አለባበስ እያንቀጠቀጠ ወዲህ ወዲያ የሚንጎራደደው ጌቱ ከሁለት ተመሳሳይ ጓደኞቹ ጋር የተንቀሳቃሽ ስልኩን ሰዓት መቁጠሪያ እየተመለከተ የመኪናውን መድረስ ይጠባበቃል:: ወዲያው መኪናው ደርሶ ሳያቆምላቸው ራሳቸው ተንጠላጥለውበት ወደ ቆሻሻ መጣያው ያመራሉ:: ቀድመው በቆሻሻ መጣያው ስፍራ ከደረሱት ተመሳሳይ ወጣቶች ቀደም ብለው ከመኪናው የሚወርደውን ቆሻሻ በቅድሚያ መፈተሽ የሚችሉት እንዲህ ከመንገድ ጀምሮ በመኪናው ላይ በመንጠልጠል ነው:: ይህ ስፍራ በእርግጥም የወጣቶቹን ጥገኝነት ብቻ አይደለም የሚያስተናግደው፤ ሴቶች፣ ሕፃናትና አልፎ አልፎ በዕድሜ ጠና ያሉ አባወራዎችንም ይሰበስባል:: አንዳች የሚነጠቅ ነገር ካለ በሚል ከሰው እኩል ቆሻሻው ላይ የሚረባረቡትና ባካባቢው ሰማይ ላይ የሚያንዣብቡት አሞሮችም ሌሎች ጥገኞች ናቸው:: ከሆቴሎች አካባቢ ከሚወጣ ቆሻሻ ውስጥ ተሸጉጠው የሚገኙ የታሸጉ ምግቦችና በቅጡ የሥጋና የዓሣ ምርቶችም የነዚህ የቆሼ ማኀበረሰብ ሁነኛ የምግብ ምንጮች ናቸው::

እንደ አንድ ትንሽ የተራራ ሰንሰለት አለፍ አለፍ ብሎ በጉብታ የተያያዘው ቆሼ በአብዛኛው በማይበሰብሱ ፕላስቲኮች፣ ጨርቆችና ጣሳዎች

የተሞላ ነው:: በውስጡ ከያዘው ርጥብ ቆሻሻ የተነሣ አካባቢው በፈሳሽ የረጠበና ረግረግ ነው:: ይህን ለማየት እንኳን የሚቀፈውን ቆሻሻ ፍሳሽ ግን እነኛ የቆሼ ልጆች በተጫሟቸው የወታደር ከስክስ ጫማዎች ያለመፀየፍ ይረግጡታል:: ሲብስም ከእጃቸው ያመለጣቸውን አስፈላጊ ዕቃ ጎንበስ ብሎ ለማንሣት እጃቸውን ይሰዱበታል:: ይህ ብስባሽና በደረቅ ቆሻሻ የተሞላው የቆሻሻ መጣያ ስፍራ በ14 ሄክታር ሜትር ላይ የሰፈረና ለከተማው ብቸኛ የቆሻሻ መጣያ ሥፍራ ሆኖ ለስድስት ዐሥርትና ከዛ በላይ ያገለገለ ነው::

ባለፉት ሃያ ዓመታትና ከዛም በፊት በከተማው የመስፋት እንቅስቃሴ ምክንያት በአካባቢው የሰፈረውን ሕዝብ ተከትሎ ቆሼ ለሰዎች ጤና ጠንቅ መሆኑ ታምኖበት የአካባቢው ነዋሪና በጤናው ዘርፍ የሚሠሩ የተለያዩ አገር በቀልና ዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ቆሼን ከማንሣት ጋር በተያያዘ ተከታታይ አቤቱታዎችን ለከተማው አስተዳደር አቅርበዋል:: “ቆሼ እናንተ ሔዳችሁበት እንጂ እሱ አልመጣባችሁም” የሚል ተደጋጋሚ ምላሽ እየሰጠ የነዋሪዎቹን አቤቱታ በእንጥልጥል ያቆየው የከተማው አስተዳደርም በከተማዋ እየተንሰራፋ የመጣውን የመሠረተ ልማት ግንባታን በአሁኑ ወሳኝ ወቅት ላይ እስከሚያገኘው ድረስ ወደ ተግባር የሚቀይረው ምንም ዓይነት የስምምነት ውል አልነበረውም:: ባለፉት ጥቂት ዓመታት መካኒሳ፣ ዘነበ ወርቅና ለቡ በተሰኙት የከተማዋ አካባቢዎች በስፋት እየተገነቡ ባሉት መንገዶች፣ የመኖሪያ ቤትና ድርጅቶች ምክንያት ግን የቆሼ እህል ውሃ ሊያበቃ ግድ ሆኗል:: ይህን የከተማውን አስተዳደር አቋም የሚያፀናው የተለዋጭ የቆሻሻ መጣያ ስፍራ ግንባታ በዘመናዊ መልኩ እንዲገነባ የሚያስችለው የመሠረተ ድንጋይም በቅርቡ በሰንዳፋ አካባቢ በ32 ሄክታር መሬት ላይ ተጥሏል::

ይህን የምስራች የሰሙት የአካባቢው

ነዋሪዎችም በጥያቄያቸው መዘግየት የተነሣ በከተማው ላይ የነበራቸውን ቅራኔ በመተው “እንኳን ደስ ያለን” እየተባባሉ ነው:: አቶ አድማሱ አበበ የቆሼ የቅርብ ጎረቤት ሆነው መኖር ከጀመሩ ሃያ ዓመታትን አስቆጥረዋል:: ወደ አካባቢው ለመኖር ሲመጡ ቆሼን ተጎራብቶ መኖሩ ከባድ እንደነበረ ቢረዱትም በወቅቱ ሌላ የመኖሪያ አማራጭ ስላልነበራቸው “ቀን እስኪያልፍ……” በሚል ፈሊጥ ኑሮአቸውን ለመመሥረት ተገደዋል:: ሆኖም ግን ይህን ያህል ጊዜ ቆሼን በአካባቢው አየዋለሁ የሚል ግምት አልነበራቸውም:: ይህ የተዛባ ግምታቸውም ዛሬ ላይ ለሸመቱት የአስምና ተያያዥ በሽታዎች ምክንያት ሆኗቸዋል:: “እኔን ጨምሮ ብዙዎች ታመናል:: ልጆቹም ጤነኞች አይመስሉኝም፤” ሲሉ ነበር:: የቆሼን የጤና ጠንቅነት በአጭሩ የገለፁት ወይዘሮ ፀሐይ ወልደ ሰንበትም ቆሼን በቅርብ የሚጎራበቱ የአካባቢው ነዋሪ ናቸው:: “ለኛ ያን ያህል ችግር የለውም፣ ለምደነዋል:: ለልጆችና ለአዛውንቶች ግን ከባድ ነው:: ምክንያቱም አየሩም ሆነ ውኃው በቀላሉ በቆሻሻ ስለሚበከል ለተዛማች አየር ወለድ በሽታዎች ይጋለጣሉ፤” ሲሉ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ:: በቆሼ ዙሪያ በሚገኙ ምዕራፍ ፋና፣ አዲስ አምባ እና ቄስ ማኅበር የተሰኙ የአካባቢው የመኖሪያ ቤት ማኅበራት አብዛኛው አባሎች በቆሼ መነሣት ከፍተኛ ደስታ ሲፈጥርባቸው ለተወሰኑት ግን ቅሬታ ይዞ መምጣቱ የማይቀር ይመስላል:: ምክንያቱ ደግሞ እነሱም ሆኑ ልጆቻቸው ኑሮአቸውን የመሠረቱት ቆሼን ተገን በማድረግ ነው:: “ከቆሼ የማይገኝ ምን አለ? ሲሉ ንግግራቸውን የሚጀምሩትና ወይዘሮ ወለቱ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ የቤት ማገዶ የሚሆኗቸውን ቀላጭ ቁሳቁሶች፣ የመመገቢያና የመገልገያ ሳህኖች፣ ውኃ መጠጫዎችና የመሳሰሉት ሁሉ ለቤት ፍጆታነት ከማገልገልም አልፎ ፀድተው ለሽያጭ የሚቀርቡ እንደሆኑ ይናገራሉ::

ለዚህ ነው ጌቱም ሆኑ ጓደኞቹ በቆሼ መነሣት ዙሪያ ለቀረበላቸው ጥያቄ አሉታዊ ምላሻቸውን የሚሰነዝሩት:: “ዋነኛ ተጎጂዎች እኛ ነን:: ሌላ ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ ሊኖረን የሚችል አይመስለኝም፤” ይላል ጌቱ:: ሌላኛው ጓደኛው በበኩሉ “በቆሼ መዘዋወር የማይጎዱት እነኚህ አሞሮች ብቻ ሊሆኑ ይችላሉ:: ምክንያቱም ክንፍ ስላላቸው ጠረኑን ተከትለው የደረሰበት ይደርሳሉ፤” ሲል በጨዋታ መልኩ አስተያየቱን ይሰጣል::

በእርግጥም በቆሼ ረዺ ዙሪያ የሚገኙ የቆሼ ጥገኞች በቆሼ ሥፍራ መቀየር የተነሣ ከፍተኛ የኑሮ መመሰቃቀል ሳይገጥማቸው የሚቀር አይመስልም:: የከተማው አስተዳደር ግን ግድ የለም ለነሱም ቢሆን ይታሰባል ይላል:: በአዲስ አበባ አስተዳደር የፅዳት ኤጀንሲ ቢሮ ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ኤርምያስ ሥዩም ለሪፖርተር እንደገለፁት ከ700 በላይ የሚሆኑ የቆሼ ተዳዳሪ ቤተሰቦችን በአዲሱ የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት ውስጥ የሥራ ዕድል መፍጠር በሚቻልበት ሁኔታ እየተሠራ ነው ይላሉ:: አዲሱ የቆሻሻ መጣያ ስፍራ ኤኤስዲ በተሰኘ የፈረንሳይ ኩባንያ ድጋፍ በዘመናዊ መልኩ የሚገነባ ደረቅና ብስባሽ ቆሻሻዎችን ከመለየት ባሻገር ቆሻሻን በድጋሚ ለአገልግሎት ማዋል በሚያስችል አሠራር ሒደት ውስጥ የሚገነባ በመሆኑ ለሰዎቹ የሥራ ዕድል ይፈጥራል:: ከዚህም በላይ ቆሻሻው ወደ መጨረሻው የማከማቻ ሥፍራ ከመድረሱ በፊት በተለያዩ የከተማዋ ቦታዎች የማቀባበያ ጣቢያዎች ስለሚኖሩት በነዚህ ጣቢያዎች ውስጥም የሥራ ዕድል መኖሩ አይቀርም ባይ ናቸው:: እንደ አቶ ኤርምያስ አገላለጽ፣ “በነዚህ ዜጎች ሕይወት ላይና በአካባቢው ላይ ስለሚፈጥረው ተፅዕኖ ጥናቱን ያካሄደው ኢንዳ ኢትዮጵያ የተባለ አቀር በቀል ድርጅት አጠቃላይ ጥናቱን አጠናቆ ለፕሮጀክቱ ጽሕፈት ቤት ሲያቀርብ ይህ ሁኔታ ተጨባጭ ምላሽ ወደሚያገኝበት ደረጃ ይሸጋገራል::”

የቆሼ መጨረሻና አዲሱ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ

Page 37: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 37 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ማስታ

ወቂያ

ማህበራዊ ማህበራዊ ማህበራዊ ማህበራዊ ማህበራዊ

የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅትክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

ተ.ቁ.የሥራ መደብ መጠሪያ

ተፈላጊ የትምህርት ደረጃና ዓይነት

በሙያው አግባብ ያለው የሥራ ልምድ

ብዛት ደመወዝ የቅጥር ሁኔታ

1 የሽያጭ ሠራተኛ

የኮሌጅ ዲፕሎማ በሽያጭ አስተዳደር

0 ዓመት 2 በስምምነት በኮንትራት

የሥራ ቦታ ……………………………… ዋናው መ/ቤት /አ.አ/

ማሳሰቢያ

አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ

ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የሥራ ልምድ

ማስረጃችሁን /ስቱደንት ኮፒ/ ከማይመለስ ፎቶኮፒ ጋር በማያያዝ የሰው

ሃብት አመራር የስራ ሂደት ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 210 ማመልከት

ይችላሉ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-15-77-79 ይደውሉ፡፡

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከዚህ በተች ባለው ክፍት የሥራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

የሥራ መደቡ መጠሪያ

ብዛትተፈላጊ የትምህርት ደረጃና የሥራ

ልምድየቅጥር ሁኔታ

ደመወዝ

ኢንፎርሜሽን እና የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት ኃላፊ

1

• ከታወቀ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ በፖለቲካል ሳይንስና ሕዝብ ግንኙነት /PSIR/፣ በማኔጅመንት፣ በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን፣ በጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን የመጀመሪያ ዲግሪ፡፡

• 6 ዓመት የሥራ ልምድ ኖሮት/ኖሯት ከዚህ ውስጥ 2 ዓመትና ከዚያ በላይ በሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የሰራ/ች፡፡

• መሰረታዊ የኮምፒውተር እውቀት ያለው/ያላት፡፡

በቋሚነት 4,750.00

• አመልካቾች የትምህርት እና የሥራ ልምድ ማስረጃቸውን ዋናውንና

የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት

ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የሰው ኃይል ዕቅድና

ምደባ ሲኒየር ኤክስፐርት ቢሮ በግንባር በመቅረብ መመዝገብ ይችላሉ፡፡

• ለፈተና የሚቀርቡ አመልካቾች በስልክ ጥሪ ይደረግላቸዋል፡፡

• ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0114-66 75 19 ወይም 0114-65 15 44

ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት

ክፍት የሥራ ቦታ

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/በሔ

ኖክ ያ

ሬድ

ፍ ሬ ና ፍ ርከ

‹‹የኢትዮጵያ ባህል ማለት የኢትዮጵያ ሕዝቦች ባህሎች ተደምረው የሚፈጥሩት ነው:: የኢትዮጵያ ቋንቋ ማለት የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በሙሉ ተደምረው የሚፈጥሩት ጉዳይ ነው:: የኢትዮጵያ ታሪክ ማለት የሁሉም ሕዝቦቻችን ታሪክ ተደምሮ የተፈጠረው ነገር ነው::››

የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት 7ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን

ኅዳር 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ‹‹ብዙም አንድም ሆነን በመለስ ራዕይ፤ በሕገ መንግሥታችን ለሕዳሴያችን›› በሚል መሪ ቃል ሲከበር ካወጣው መግለጫ

በሔኖክ ያሬድ

“ብሔር ብሔረሰቦች

ኑ ኑ የኢትዮጵያ ልጆች …”

የሚለው በታዳጊዎች ድምፅ እየተንቆረቆረ በየጊዜው የሚሰማው በተለይም ጎልቶ የሚደመጠው በአዲሱ ሕዝባዊ በዓል የብሔረሰቦች ቀን ነው::

“ኅዳር 29 ቀን” እንደ ሌሎች ሃይማኖታዊና መንግሥታዊ በዓላት መሥሪያ ቤቶች ተዘግተውለት የመከበር ዕድል ባይገጥመውም በዓሉ ኅብረተሰቡ በሚኖርበትና በሚሠራበት፣ በሚማርበትም ልዩ ልዩ ተቋማት ውስጥ ሆኖ ይከበራል:: ከ1999 ዓ.ም. ወዲህ በአገር ደረጃ በሚመረጡ የክልሉ ከተማ በዓሉ መከበር ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ ዘንድሮ ሰባተኛው በዓል ላይ ደርሷል:: በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት የሚከበረው በዓል 2005 ላይ ከየክልሉ

“ይቺ ቀን …”

የመጡ የየብሔረሰቡ ተወካዮች የተሳተፉበትን በዓል የአማራ ክልል መዲና ባሕር ዳር አስተናግዳ ነበር::

በፌዴራል ደረጃ በዓሉ ባሕር ዳር ይከበር እንጂ በሁሉም የአገሪቱ ከተሞች በልዩ ልዩ ዝግጅት መከበሩ አልቀረም:: የአዲስ አበባ ልጆች በተለይም ተማሪዎች ዕለቱን ያሳለፉት በየትምህርት ቤቶቻቸው ባዘጋጇቸው ጥበባዊ ዝግጅቶች ብቻ የተወሰነ አይደለም:: በተለይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከግቢያቸው ውጭ በተለያዩ የባህል ቤቶች ኅዳር 29ን አድምቀው ታይተዋል:: ከእነዚህ መካከል ዳግማዊ ምኒልክ ቤተ መንግሥትን (ታላቁ ቤተ መንግሥት) የተጎራበተው ቅዱስ ገብርኤለ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ይገኙበታል::

የአዲስ አበባ ጥንታዊ ሰፈር በሚገኝበት “ውቤ በረኻ” በደጃች ውቤ ቅጥር ግቢ በሚገኘው የአሁኑ “አዲስ አበባ ምግብ ቤት” 40 የሚደርሱ ሴትና ወንድ

ተማሪዎች በተለያዩ ብሔረሰቦች አልባሳትና መዋቢያ ቁሳቁሶች ጭምር ተውበው በባህላዊ ምግብና ባህላዊ ሙዚቃ ምግብ ቤቱን አድምቀውት ነበር::

“ይቺ ቀን የባህል ቀናችን ናት:: የምንከብርባት፣ የምናከብራት ቀናችን ናት” በማለት አስተያየቱን የሰጠን የ12ኛ ክፍል ተማሪው ናትናኤል ዘነበ ነው::

ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ኅዳር 29 ቀን የተከበረው “ብዙም አንድም ሆነን በመለስ ራዕይ፤ በሕገ መንግሥታችን ለሕዳሴያችን” በሚል መሪ ቃል ነበር::

የብሔረሰቦች ቀን ኅዳር 29 ቀን መከበር የጀመረው ኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊኳን የመሠረተችበትን ሕገ መንግሥት ያፀደቀችበት ቀን በመኾኑ ነው:: ሪፐብሊኩ ከተመሠረተ ዘንድሮ 18ኛ ዓመቱን ሲይዝ ሕገ መንግሥቱም ሙሉ በሙሉ በሥራ ላይ የዋለው ከነሐሴ 15 ቀን 1987 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑ ይታወቃል::

የራዲካል አካዳሚ ተማሪዎች በዓሉን በአዲስ አበባ ምግብ ቤት ተሰባስበው በቦረና ኦሮሞ ባህላዊ አለባበስና አጋጊያጥ ተውበው ሲያከብሩ

የቅዱስ ገብርኤል ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የዘንድሮው የብሔረሰቦች ቀን በአዲስ አበባ ምግብ ቤት ያከበሩት በበርካታ ብሔረሰቦች አልባሳትና ጌጣጌጥ ተውበው ብቻ ሳይሆን ባህላዊ

ሙዚቃዎችን ከነዳንኪራቸው በመጫወት ጭምር ነበር

Page 38: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 38|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

ከህዳር 5-7 ቀን 2005 ዓ.ም. በጅቡቲ በተካሄደው 39ኛው የእስላማዊ ትብብር ድርጅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ካዛክስታን ለረዥም ጊዜያት የቆየውን የማህበሩን ሊቀመንበርነት ለተተኪው አስረክባለች:: ከሰኔ 2004 እስከ ህዳር 2005 ዓ.ም. ለአንድ ዓመት ተኩል ያህል ድርጅቱን በሊቀመንበርነት ያገለገለችው የማዕከላዊ ኤስያዊት አገር የአገልግሎት ጊዜዋ አጭር ተደርጎ ሊወሰድ ቢችልም ድርጅቱን ስትመራ ከገጠሟት ተግዳሮቶች አንፃር ግን ረዥም የሚባል ነበር::

እንደሚታወቀው እ.ኤ.አ ከ2011 እስከ 2012 ድረስ በእስላማዊ ዓለም የተፈጠሩት ሁነቶች አስቸጋሪ ሆነው ስለመከሰታቸው የሚካድ አይደለም:: በተለይ በመካከለኛው ምስራቅና በሰሜን አፍሪካ የተከሰቱት ድራማዊ የፖለቲካ ክንውኖች ድርጅቱን በመምራት ጫና ውስጥ ለነበረችው ካዛክስታን በጣም ከባድ ነበር:: ይህ ሁሉ ፖለቲካዊ ቀውስ ድርጅቱንም ሆነ የድርጅቱን መሪ አገር ለተፈጠረው ቀውስ አፋጣኝና በቂ መፍትሄ እንዲፈልጉ ያስገደደም ነበር:: በመሆኑም አሁን ያለውን ሁኔታ ስንመለከት ድርጅቱም ሆነ ኃላፊነቱ የወደቀባት አገር በአካባቢው የተፈጠረውን ቀውስ ከማርገብና ከመቆጣጠር አንፃር እጅግ ውጤታማ ሥራ ማከናወናቸውን ነው:: ይህም ውጤት የድርጅቱን ዋና ፀሐፊ ኢክሜሌዲን ኢህሳኖግሉ ካዛክስታን የእስላሙን ዓለም የገጠሙትን ፈታኝ ሁነቶችን በመቆጣጠር፣ ውሳኔ በመስጠትና ለመፍትሔ በመትጋት ደረጃ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጭብጦች ላይ እንደ አገር የተጫወተችውን ሚና በሁሉም አባል አገራት ከፍተኛ እውቅና እንዳገኘ እንዲረዱት አስችሏቸዋል::

የካዛክ ሊቀመንበርነት በአጭር ጊዜ ውስጥ በእስላማዊ አገሮች ዘንድ ተቀባይነት የነበራቸውን በራስ ተነሳሽነት የተረቀቁ ጅምሮችንና ፖሊሲዎችን ወደፊት ለማራመድ ሞክሯል:: ከእነዚህ ጅምሮች መካከል በካዛክስታን መዲና አስታና ውስጥ መሠረቱን ያደረገውና የድርጅቱ የምግብ ዋስትና ቢሮ አንዱ ነው:: የዚህን ውጥን ተግባራዊነት በወደፊቱ መነጽር ስንመለከት የእስላም አገሮችን የምግብ ዋስትና ዘለቄታዊ በሆነ መንገድ ለረዥም ጊዜ የሚደገፉ ይሆናል::

ወጥ በሆነ መልኩ እያደገ የመጣው የካዛክስታን በእስላሙ ዓለም የምትጫወተው ሚና ድርጅቱ ዋና ከተማዋን አስታናን ጨምሮ በቀጣይ ጥቂት ዓመታት ውስጥ በአምስት የተለያዩ የዓለም ከተሞች ክልላዊ መቀመጫዎችን ለመመሥረት ካለው እንቅስቃሴም ጋር ይያያዛል:: የዚህ ቢሮ በከተማዋ መከፈት ከተማዋ በሂደት የዓለም አቀፍ ድርጅቶች የአባቢያዊ ማህበራት መናኸሪያ እንዲያደርጓት ይጠበቃል::

እንዲህ ያለ ዕድልን አግኝቶ የድርጅቱ አካባቢያዊ ጽ/ቤትን ይዞ በርካታ ላይ መገኘቱ ድርጅቱ ከሌሎች ማዕከላዊ ኤስያ ሀገራት፣ ኮውከሰስ፣ ኢራን፣ ራሽያና ቻይና የሚኖረውን የድርጅቱን ግንኙነት የበለጠ የሚያቀለውና ውጤታማም የሚያደርገው ይሆናል::

በካዛክ ሊቀመንበርነት ስር እስላማዊ ድርጅቱ በታሪኩ የመጀመሪያ የሆነውን የአባል አገራቱን የፓርላማ ምርጫዎችን ለመታዘብ በሊቀመንበሯ አገር አመራር የታዛቢነት ተልዕኮዎች እንዲያከናውኑ ሆኗል:: በተለይም እ.ኤ.አ. በጥቅምት 2011 በቱኒዚያ እና በወረሃ ግንቦት 2012 በሊቢያ የተከናወኑ የፓርላማ ምርጫዎችን በካዛክስታን የተመራ የታዛቢ ቡድን ተሰማርቶ ነበር::

የእስላማዊ ትብብር ድርጅቱ ሊቀመንበርነት የካዛክስታንን የውስጥ ድርጅቶችና ማህበራትን የማዋቀር ልማድ እንዲጠናከር አድርጎታል:: ቀደም ሲል አገሪቱ በአውሮፓ የፀጥታና ትብብር ድርጅት ሊቀመንበርነትና የሻንጋይ የትብብር ድርጅትን ጨምሮ በሌሎቹም መሰል ድርጅቶች የነበሩትን ልምድና ተሰሚነት በመጠቀም ከእስላማዊ ድርጅቱ ጋር ግንኙነት እንዲመሠርቱ አስችለዋል::

በካዛክስታን ሊቀመንበርነት ወቅት በድርጅቱ ውስጥ የተቋቋመው የሰብዓዊ መብቶች ቋሚና ገለልተኛ ኮሚሽን አንዱ ሲሆን ኮሚሽኑ ሁለት አጠቃላይ ስብሰባዎችን ያደረገው በካዛክስታን የሊቀመንበርነት ጊዜ ነበር:: የዚህ ኮሚሽን መቋቋምም ድርጅቱ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮችን ተቀዳሚ አጀንዳ በማድረግ ከሌሎቹ ዓላማዎቹ ጋር አብሮ

እንዲሰራባቸው የሚያሰችል እምርታም ነው:: በአጠቃላይ በካዛክስታን የድርጅቱ ሊቀመንበርነት ወቅት ድርጅቱ

አርባ ያህል ስብሰባዎችን ከእነዚህ ውስጥ የድርጅቱ የበላይ አመራሮች ጉባዔዎች፣ ተከታታይ የድርጅቱ የጤና፣ የአካባቢና የሳይንስ ሚኒስትሮች ኮንፈረንሶች ይገኙባቸዋል::

ሲጠቃለልም የካዛክስታን ዋና ከተማ አስታና የእስላማዊ ትብብር ድርጅቱ በሰኔ 2011 (እ.ኤ.አ.) በከተማዋ ባደረገው አጠቃላይ ጉባዔ ከ40 ዓመታት በላይ የነበረውን የእስላማዊ ኮንፈረንስ ድርጅት የሚለውን የቆየ መጠሪያ የእስላማዊ ትብብር ድርጅት በሚል አዲስ መጠሪያ የተሰየመባት በመሆኗ ለዘለዓለም ስትታወስ ትኖራለች:: ይህ ድርጅቱን ከታላቁ የተባበሩት መንግሥታት ቀጥሎ የላቀ የሚያደርገውን ዓለም አቀፋዊ ድርጅትነት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስተዋውቅ በመሆኑ በታሪካዊነቱም ሲወሳ ይኖራል::

ካዛክስታንና ዓለምአቀፍ ፀረ-ኒውክለር ዘመቻ

እ.ኤ.አ. በነሐሴ 2010 በካዛክስታን ተነሻሽነትና በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ ድጋፍ የኒውክለር መሳሪያዎችን ሙከራ የሚፃረረውን ዓለምአቀፍ የእርምጃ መውሰጃ ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ በካዛክስታን ተከብሯል:: ይህ ቀን ከ19 ዓመታት በፊት የካዛክስታኑ ፕሬዝዳንት ኑር ሱልታን ኖዛር ባዬቭ በትልቅነቱ ከዓለም በሁለተኛ ደረጃ ይቀመጥ የነበረውንና በካዛክስታን የሚገኘውን የሴሚ ፓለቲንስክ የኒውክለር መፈተሻ ማዕከልን ለመዝጋት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ የፈረሙበት ዕለት ነበር:: በቀድሞው የሴሚ ፓላቲንስክ ፍተሻ ማዕከል የመጨረሻ የነበረው የኒውክለር ጫኝ መርከብም የወደመው እ.ኤ.አ. ግንቦት 7 ቀን 1995 እና ሐምሌ 29 ቀን 2000 ነበር:: በዚሁ ወቅት ነበር የመጨረሻው የኒውክለር መሞከሪያው ዋሻው የፈነዳው:: የኒውክለር ሙከራን የሚያግደው ህግ በተግባር ላይ መዋሉ አሰቃቂ ሁነቶችን በህይወታቸው አይተው ላለፉት የካዛክስታን ሕዝቦች ትልቅ ትርጉም ነበረው:: በአርባ ዓመታት ውስጥ 450 የኒውክለር ሙከራዎችን ያስተናገደው የሴሚ ፓላቲንስክ የሙከራ ጣቢያ ለአንድና ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ ስቃይ ምክንያት ሆኖ አልፏል::

ከሴሚ ፓላቲንስክ የኒውክለር መሞከሪያ ጣቢያ መዘጋት በኋላ ነበር ከኒውክለር ነፃ ካዛክስታን አዲስ ዘመን የጀመረው:: ይህም ከሶቭየት ሕብረት መፈራረስ በኋላ የኒውክለር መሣሪያዎችን በጠቅላላ ለማውደም የተደረሰበትን ወሳኝ ጉዞ ያፀደቀው የአዲሱ መንግሥት የተጠና ውሳኔ ነበር:: ስለዚህም የዚህች አዲስ ተወላጅ አገር የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ከኒውክለር የፀዳ ዓለምአቀፋዊ መርህ በተሰኘው የህግ ማዕቀፍ ውስጥ እንዲፀና ረድቷል:: በዚህ ረገድ ማንም የካዛክስታንን ፀረ-ኒውክለር አቋም በቁርጠኝነት ሊወስድ ይችላል:: ወደ ታህሳስ 1903 ስንመለከትም የካዛክስታን ከፍተኛ ምክር ቤት በኒውክለር መሣሪያ መቀነስ ላይ የፈረመውን ስምምነት እናያለን:: ከ1994 ጀምሮም የዓለምቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ አባል በመሆን በስሯ ያሉትን የኒውክለር ማልምያዎችን በኤጀንሲው ቁጥጥር ስር አድርጋለች:: የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በመስከረም አ996 (እ.ኤ.አ.) በኒውክለርና ሙከራ ላይ ያስቀመጠውን ገደብ ተግባራዊ በማድረግም ስምምነቱን በአገሪቱ ህግ ውስጥ አፅድቃ ለስምምነቱ ተፈፃሚነት ያላሰለሰ ጥረት

ካዛክስታን የእስላማዊ ትብብር ማህበር (ድርጅት)ን ሊቀመንበርነት አስረክባለች፡፡

ማስታወቂያ

Page 39: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 39 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

በማድረግ ላይ ትገኛለች:: በ2006ም ከሌሎች የሰሜን ኤስያ አገራት ጋር በመሆን ካዘክስታን የተፈራረመችው የሴሚ ፓለቲንስክ ነፃ-ኒውክለር ዞን ለአካቢው የፀጥታ መጠናከርም ቁልፍ ምክንያት ሆኗል:: ይህ ስምምነት እ.ኤ.አ. በመጋቢት 21 ቀን 2004 ወደ ትግበራ ተለውጧል:: ይህን ውጤታማ አካባቢያዊ ስምምነትም የዓለምአቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ለዓለምአቀፉ የኒውክለር ቅነሳና ለፀረ-ኒውክለር ዘመቻ ከፍተኛ አስተዋጽአ ያለው ሲል አወድሶታል::

ይሁንና እነዚህ አካባቢያዊ ድርድሮች በራሳቸው በቂ ባለመሆናቸው በዓለምአቀፉ ደረጃ ሊተገበሩ ይገባቸዋል:: ስለሆነም ፕሬዝዳንት ኑር ሱልጣን ዛር ባዬቭ ዓለምአቀፍ ነፃ-የኒውክለር ስምምነት እንዲፈረም በሚያዝያ 2010 ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በተካሄደው አለምአቀፉ የኒውክለር ደህንነት ጉባዔ ላይ ሃሳብ አቅርበዋል:: ከዚህ በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ በዓለምአቀፉ ደረጃ ተግባራዊ የሚሆን የጎንዮሽና የቀጥታ የኒውክለር ቅነሳ አዲስ ስምምነት እንዲፈረም አገሪቱን አግባብተዋል:: በተመሳሳይ ሁኔታም ካዛክስታን በዓለምአቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ስር የተቀመጡትን መስፈርቶች ባሟላና ገደቡን በጠበቀ መልኩ እያንዳንዱ አባል አገር ለሰላማዊ የኃይል ፍጆታ የኒውክለር ኢነርጂን የመጠቀም መብቱ የማይኮድና ሉዓላዊ መሆኑንም ትደግፋለች:: እንደ ግንባር ቀደም ዩራኒየም አምራች አገርም ለሰላማዊ የኒውክለር ማልምያ ፕሮጀክቶች አስተዋጽኦ የማድረግ ፍላጎትም አላት:: በዚህ ዓላማ መሠረትም በግዛቷ ዓለምአቀፉ የኒውክለር ነዳጅ ክምችት ለማሰናዳት ትፈልጋለች:: ይህን አስመልክቶም «የእኛ ፍላጎት ካዛክስታን የዓለም የኒውክለር ነዳጅ ክምችት በማሳደግ አገራት ያላቸውን የኒውክለር አቅም ለሰላማዊ የእድገት ዓላማ እንዲጠቀሙበት ነው:: ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ አገራት ያላቸውን የኒውክለር ኃይል ለልማት መጠቀም እንደሚችሉ የሚገልጸውን ህግ ተመስርቶ» ነው ሲሉ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት በዋሽንግተኑ ጉባዔ ላይ ተናግረው ነበር:: የዚህ የኒውክለር ኃይል ክምችት ዋና ዓለማውም ሐብቱ ለሌላቸው አገራት የኃይል ምንጭ ሆኖ በማገልገል አካባቢያዊ፣ የኢኮኖሚና የፀጥታ ትስስርን መፍጠር ነው:: በዚህም በኩል ክምችቱ በአገሪቱ ላይ የሚያመጣው ምንም ዓይነት አካባቢያዊ ተጽዕኖ እንደለለ ተረጋግጧል:: እንደ ዓለም አቀፍ ኤክስፐርቶች አስተያየት ካዛክስታን የሬዲዮ-አክቲቭ ቁሶችን የሚያጣራ፣ የሚያብላላና የሚያከማች ቴክኖሎጂን አግኝታለች:: ይህንንም ተግባሯን በቅርብ የሚከታተለው መሆኑን የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ አስታውቋል::

«ካዛክስታን የኒውክለር ማከማቻውን በግዛቷ ለመትከል ብቸ ሳይሆን ለተከለችው ማከማቻም ተገቢውን ቁጥጥር እንደምተደርግ አረጋግጥላችኋለሁ::» ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አገራቸው በኤጀንሲው የተጠቀመጠውን የኒውክለርን ሰላማዊ ግልጋሎትና ለጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች የሚውልበትን መንገድ ቀላቅላ እንደማትጠቀም ያረጋግጣሉ::

በመሆኑም ካዛክስታን በዓለም አራተኛ ደረጃ የሚያሰጣትን የኒውክለር የጦር መሣሪያ በፈቃደኝነት በማውደምና ከአለም አቅፍ ፀረ-ኒውክለር ማህበረሰብ ጋር በመተባበርና ለሰላማዊ ልማት ብቻ የኒውክለር ኢንርጂዋን ለመጠቀም በመወሰን በጉዳዩ ላይ ያላት አቋም ሚዛናዊ፣ ዘለቄታዊና ኃላፊነት የተሞላበት መሆኑን ታረጋግጣለች::

የመካከለኛዋ ኤስያ ትልቅና ከፍተኛ የምጣኔ ኃብት ዕድገትን የምታልም በሚል የምትታወቀው ካዛክስታን ራሷን ካደጉት አገራት ጋር ለማስተካከል ባላት ከፍተኛ ጉጉትም ይህንን መጠሪያዋን ጠብቆ ለማቆየት የመንግሥቱ ፖሊሲ የሆነውን ይህን የዕድገት ራዕይ አንግባ ትንቀሳቀሳለች:: ታላላቅ ዓለም አቀፍ መድረኮችና ኮንፈረንሶችን በመደበኛነት የምታስተናግደው ካዛክስታን የአውሮፓ የፀጥታና ትብብር ድርጅትንና የእስላማዊ ትብብር ድርጅትን ጨምሮ በሊቀመንበርነት የምትመራም እንደመሆኑ የምታልመውን ግብ ለማሳካት የሚያስችል ሁኔታ ላይ እንደምትገኝም ያመለክታል:: በዚህ ረገድ የ2017ቱን ዓለም አቀፉን ኤክስፖ ለማዘጋጀት ጥያቄ ማቅረቧ በማዕከላዊ ኤስያ መሪ የምጣኔ ሀብት የኃይል ሚዛንን የምትጨብጥበትን ወሳኝ እርምጃ እንድትያያዝ ያስችላታል:: ይህ ከፍተኛ ትኩረትን የሚስብ ዓለም አቀፋዊ ትዕይንት በመዲናዋ አስታና ከተካሄደም በማዕከላዊ ኤስያ ብቻ ሳይሆን የቀድሞ የሶቭየት ሕብረት በነበረው ጠቅላላ ግዛት የመጀመሪያው ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል::

የ2017ቱን ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ለማዘጋጀት ካዛክስታን በሰኔ 10 ቀን 2011 ነበር ፓሪስ ውስጥ ለሚገኘው የዓለም አቀፍ ኤክስፖዚሽን በአገሪቱ ቋሚ ወኪል አማካኝነት ለድርጅቱ ዋና ፀሐፊ የማዘጋጀት ጥያቄዋን ያቀረበችው:: በዚህም መሠረት የኤክስፖው ቢሮ በ157 የቢሮው አባል አገራት የተሰጠውን ድምፅ ቆጥሮ የመጨረሻውን ውሳኔ በታህሳስ 2012 ተሰጥቷል::

ካዛክስታን ከ1997 (እ.ኤ.አ.) ጀምሮ የዓለም አቀፍ ኤክስፖዚሽን ቢሮ አባል ስትሆን ከ2005 (እ.ኤ.አ.) ጀምሮም በተከናወኑ ዓውደ ትዕይንቶች ተካፋይ ነች:: ምንም እንኳን በቢሮ ውስጥ ረዘም ያለ የአባልነት ታሪክ ባይኖራትም ካዛክስታን በቢሮ ውስጥ እንዲኖራት በምትፈልገው አንፀባራቂ የተሳትፎነት ሚና የተነሳ ቁርጠኛ አቋም ያላት ናት:: ስለዚህም አገሪቱ ከ2005 ጀምሮ በቢሮው ውስጥ የምታደርገው እያንዳንዱ እንቅስቃሴ የካዛክስታን ብሔራዊ የኤክስፖ ዘርፉ በኤግዚቢሽኑ እያሳየ ያለውን መነቃቃት በግልፅ ያሳያል:: በጃፓን በተካሄደው ኤክስፖ 2005 የካዛክስታን የማሳያ ቦታ 324 ስኩየር ሜትር ነበር:: ይሁንና ግን በሳራጎሳ እና ሻንጋይ በተዘጋጁት ኤክስፖ 2008 እና ኤክስፖ 2010 የካዛክስታን አጠቃላይ የማሳያ ቦታ (የዓውደ ርዕይ) ማዕከል 590 እና 1500 ስኩየር ሜትር ደርሶ ነበር:: ከዚህ በተጨማሪም በሳራጎሳ ስፔን በተካሄደውና 104 አገራት በተሳተፉበት ኤክስፖ የካዛክስታን ዓውደ ርዕይ በውስጣዊና ውጫዊ የብሔራዊ ዓውደ ርዕይ ገጽታ 3ተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች::

በ2017ቱ ኤክስፖ ካዛክስታን ይዛው እንድትመጣ እየተዘጋጀ ያለው ዓርማ (መመሪያ) «የነገው ኃይል» (ኢንርጂ ኤንድ ዘ ፊውቸር) ይሰኛል:: ይህም አገሪቱ በብዛት የያዘችውን የኃይል አማራጭ በተሰሩም የነዳጅ ዘይት፣ ጋዝንና ዩራኒየምን የምታስተዋውቅበት ትክክለኛ አማራጭ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ነው::

በመሆኑም የኃይል አቅርቦቱ ያላቸው አገራት ብቻ ሳይሆኑ የዚሁ ኃይል አቅርቦት ተጠቃሚ የሆኑ አገሮች ሁሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተሟጠጠ የመጣውን የነዳጅ ኃይልን ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህንን መፈክር ይጋሩታል የሚል ተስፋ አለ:: በዓለም አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ የመጣውን የነዳጅ ቁፋሮን ዋጋና በተቃራኒው ደግሞ እየጨመረ የመጣውን የነዳጅ ዋጋ ከግምት ውስጥ በማስገባት ዓለም የኃይል አማራጮችን እየፈተሸ እንደሚጠቀም ይጠበቃል:: ለዚህ ነው ካዛክስታን ይህን መፈክር አንግባ የ2017ቱን ኤክስፖ ለማዘጋጀትና መልካሙን አጋጣሚ ከመፍጠር አንፃር ለዓለም እነዚህን አዳዲስ የኃይል ምንጮች የሚፈጠሩበትን የመጨረሻውን ስኬት ለማሳየት የፈለገችው::

በዚህ አጋጣሚም የኤክስፖውን ጨረታ ካዛክስታን ማሸነፏን በደስታ እንገልፃለን::

የካዛክስታን የ2017ቱን ኤክስፖ ላዘጋጅ ጥያቄ

ማስታወቂያ

Page 40: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 40|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005ማስታወቂያ

Kazakhstan ended its Chairmanship at the

Organization of Islamic Cooperation

The 39th session of the Organization of Islamic Cooperation (OIC) of Foreign Ministers, which is held in Djibouti on November 15-17, 2012, ended a long lasting Chairmanship of Kazakhstan in this Organization. Almost one year and a half this Central Asian country was chairing the OIC, namely, from June of 2011 up to November of 2012. However, the time length of the chairmanship is not as much important as the matters Kazakhstan had to deal with, while chairing the OIC.

It is hard to deny that 2011-2012 years appeared to be very eventful for the Islamic world, in particular making the Kazakh Chairmanship to coincide with well-known dramatic political events in the Middle East and North Africa. This political turbulence forced the OIC and its Chair country to react timely and adequately. And now it seems that the Chair country was quite successful to manage the OIC within this extremely turbulent piece of time. That outcome probably made the OIC Secretary General Ekmeleddin Ihsanoglu to admit that Kazakhstan is perceived by all OIC Member States as a country, able to impact effectively upon decision-making process on various political and socio-economic issues, challenging the Islamic Ummah.

Within a short period of time the Kazakh chairmanship managed to push forward some of its initiatives, already welcomed by Islamic countries. Among these initiatives are, in particular, an establishment of the OIC new institution, namely the OIC Office on Food Security with the Office headquarter to be based in Astana, the capital of Kazakhstan. Putting in practice of that initiative may significantly increase in the long-run the food security of Islamic countries.

The steady growth of Kazakhstan’s involvement into Islamic world related matters can be also demonstrated by the fact that Astana is among six world capitals, where the OIC is intending to open its new regional offices in the years to come. Opening of such office in Astana is likely to contribute drastically to the city’s gradual transformation into the hub for international organizations regional offices. Appearing an a map as such a hub is a long-lasting Kazakh ambition and establishment of the OIC regional office in Astana will ease the coordination of the OIC relationship with Central Asia countries, Caucasus, Iran, Russia and China.

Under the Kazakh chairmanship the OIC practiced first time ever dispatching its observation missions under the guidance of a Chair country to the OIC Member States to monitor there parliamentary elections. In particular, Kazakhstan representatives led the OIC observation missions for monitoring parliamentary elections in Tunisia in October 2011 and in Libya in May of 2012.

The Chairmanship at the Organization of Islamic Cooperation really stressed Kazakhstan’s experience to run massive international organizations. The previous Kazakh chairmanship at the Organization for Security and Cooperation in Europe, Shanghai Cooperation Organization and others enabled the country to establish some cooperation links of the OIC with these influential international associations.

Among other the OIC related events within the Chairmanship of Kazakhstan one is to mention the establishment of the OIC Independent Permanent Commission on Human Rights, which already held two of its meetings within the term of the Kazakh Chairmanship. Establishment of such a Commission might be a big step forward towards bringing human rights issues into the agenda of the OIC activities.

Overall, within the term of the Chairmanship of Kazakhstan the OIC held roughly 40 events, among which were several the OIC Executive Committees meeting, the range of OIC ministerial conferences on health, environment and science.

In conclusion it is to be stressed that Kazakhstan’s capital Astana will always be commemorated as the venue, where in June of 2011 the Organization of Islamic Cooperation got its new title, which replaced almost 40-years existing title of the Organization of Islamic Conference. Adoption of the new title and logo by the second after the UN biggest international Organization is indeed to be regarded as the genuinely historical event.

Kazakhstan, which is widely known as the biggest and economically most ambitious country of Central Asia, emphatically does its best to keep this image, what is a part of the Government’s policy to make Kazakhstan join the community of the world’s most developed nations. Internationally massive forums and conferences regularly held in Kazakhstan, as well as the country’s earlier and current chairmanship at various international organizations, such as the Organization of Security and Cooperation in Europe (OSCE) and the Organization of Islamic Cooperation and some others do really meet this ultimate goal. In this regard, the bid of Kazakhstan to host in 2017 the EXPO World Exhibition seems to be another massive step towards securing the country’s position of being a leading economic power in Central Asia. To say that, it worthwhile to stress that EXPO-2017, if to be held in the Kazakh capital Astana, would be the first international exhibition of this kind not only in Central Asia region but across the entire area of the former Soviet Union.

In June 10, 2011 Kazakhstan officially articulated its bid to host the EXPO-2017 in Paris based Bureau of International of Expositions. The official Kazakh representatives submitted to the Secretary General of the Bureau the bid of Kazakhstan. But only in December of 2012 the Bureau of International Exhibitions will adopt a final decision on the host country of the EXPO-2017, after the calculation of votes by 157 Member States of the Bureau.

Kazakhstan has been a member of the Bureau of International Expositions. since 1997 and takes part in the EXPO events since 2005 and onwards. Evidently this is not a long history of Kazakhstan’s participation in this event but it is hard to deny the Kazakh devotion to be

among its brightest participants. Thus, every new case of Kazakhstan’s involvement into the EXPO since 2005 made it clear the visible enlargement of the Kazakh national sector at the Exhibition. Tat the first case in EXPO-2005 in Japan the Kazakh exposition area was about 324 sq. m, whereas in EXPO-2008 and EXPO-2010 in Saragossa and Shanghai Kazakhstan’s exposition area totaled 590 and 1500 square meters respectively. Furthermore, in Spanish Saragossa the Kazakh exposition was awarded out of 104 states by the 3rd Prize for the quality of internal and external embellishment of the national exposition.

The slogan of the EXPO-2017, being proposed by Kazakhstan is “Energy of the Future”, which definitely seems to be a right choice for a country endowed with enormous natural energy resources, namely oil, gas and uranium. However, not only energy producing countries, but also the consuming nations undoubtedly must share the concern of what the world might become after the depletion of oil and gas reserves worldwide. Keeping in mind that oil extraction rates are decreasing and its price steadily grows, the world is expected to start using alternative sources of energy. This is why Kazakhstan’s bid to host EXPO-2017 under such slogan might be a good opportunity for the world to witness the latest achievements in creating these new sources.

Kazakhstan is indeed a relatively new country and it is hard to predict what would be the final decision of the Bureau of International of Expositions on the EXPO-2017 in December of 2012. But regardless of what it might be the ambitions of Kazakhstan to host EXPO-2017 in Astana are worthy to be considered seriously.In that regard, we are proud to announce that we have been selected to host the EXPO-2017.

In 2010, August 29 at the initiative of Kazakhstan and supported by the UN General Assembly International Day of Action against nuclear testing was celebrated internationally first time. That day 19 years ago the President of Kazakhstan Nursultan Nazarbayev signed a Decree on closing the Semipalatinsk nuclear test site, that was the second in the world in terms of its size and located in Kazakhstan. The last nuclear warhead was destroyed at the former Semipalatinsk Test Site on May 7, 1995, and on July 29, 2000 the same test site was the place, where the last tunnel for conducting nuclear tests was exploded.

The issue of total ban of nuclear tests was of particular significance for people of Kazakhstan, who experienced their horrors. During 40 years 450 tests were carried out at the Semipalatinsk test site, which made to suffer one and half million people.

After the closure of the Semipalatinsk nuclear test site began the era of nuclear-free Kazakhstan began. That was a deliberate option of a young state government that made a decisive step towards a complete renunciation of nuclear weapons, which remained in Kazakhstan after the Soviet Union collapse. Thus, foreign policy of a newly-born country relied upon principles of moving towards the world free of nuclear arms. In this regard one can determine the main stages of Kazakhstan’s strategy of nuclear-free world. Back in December 1993, the Supreme Council of Kazakhstan ratified the Treaty on the Nonproliferation of Nuclear Weapons (NPT). Since February 1994, Kazakhstan became a member of the IAEA and transferred all its nuclear facilities under Agency’s control. After the UN General Assembly voted in September 1996 for the Comprehensive Nuclear Test Ban Treaty (CTBT), which became the cornerstone of international security and nuclear non-proliferation, Kazakhstan also ratified this document and became active participant in all activities undertaken within the framework of its practical implementation. In 2006 Kazakhstan, along with other Central Asian countries signed the Semipalatinsk Treaty on a Nuclear-Free-Zone in Central Asia that became an important contribution to strengthening regional security. On 21st of March 21, 2009 the Treaty entered into force. The IAEA identified the Treaty as a real contribution to the implementation of the Treaty on the Nonproliferation of Nuclear Weapons (NPT) and the global process of disarmament and nuclear non-proliferation.

However, sometimes regional initiatives are not enough and they need to be lifted to the global level. Therefore, in April 2010, Nursultan Nazarbayev proposed at the global nuclear security summit held in Washington to adopt a Universal Declaration of the world, free of nuclear weapons. In addition, President Nazarbayev initiated signing of a new Treaty on global horizontal and vertical non-proliferation of nuclear weapons.

At the same time, Kazakhstan supports the legitimate and inalienable right of every member-state of the NPT to develop and use peaceful nuclear energy under compliance with all requirements of the IAEA.

Kazakhstan, being one of the largest uranium producers in the world, intends to contribute to development of peaceful nuclear energy industry. With that aim Kazakhstan is ready to host international nuclear fuel bank on its territory. This was sounded in 2009 by the Kazakh President Nursultan Nazarbayev. “Our initiative to place in Kazakhstan international nuclear fuel bank is a tangible contribution of Kazakhstan strengthening the nonproliferation regime, the removal of those” white spots, which exist in international law on the right of some countries to develop their own national national programs for the use of peaceful nuclear energy”, - noted in this regard the President of Kazakhstan.

The primary objective of the bank is to provide countries, which wish to develop peaceful nuclear energy but lack sufficient domestic resources the access to nuclear materials. In this case the bank does not pose any environmental threat to the country. According to international experts, Kazakhstan has secure technologies for extraction, processing and storage of radioactive materials. The IAEA also promises to ensure its control over the bank’s functioning.

“Kazakhstan is ready not only to place the bank in its territory, but also to ensure proper storage of nuclear fuel”, - said Nursultan Nazarbayev, “I can assure you that Kazakhstan will never cross the line separating peaceful and military nuclear programs.”

Thus, Kazakhstan voluntarily renounced the world’s fourth nuclear arsenal and appears to be a reliable partner of the international community on issues, related to nonproliferation, disarmament and peaceful use of atomic energy. Politics of Kazakhstan in these matters remains well-balanced, consistent and responsible.

Kazakhstan and global nuclear disarmament

Kazakhstan’s bid to host EXPO-2017

Page 41: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 41 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

አሰናጅ፡- ሔኖክ ያሬድ

“የዚህ ዓለም መስፈሪያ ቁና ወይም መዳልው ሰው ራሱ ነው” አለ ከነዚህ አንዱ ፕሮታጎራስ የሚባለው:: ይህንን አስተሳሰብ በእምቢተኛ (ሬቤል) ጎረምሳ መንፈስ መስለው ያቀረቡ ታሪከኞች አሉ:: “የተረት ዘመን” የሚባለውን ደሞ በልጅነት:: በአንጻሩ ሶክራቲስ ግን “ግኖሲ ሳፍቶን ራስህን ዕወቅ” ሰባቱ ጥበበኞች ከሚባሉት አንዱ የቀረጸው መፈክር መሆኑ ይነገራል:: የጥንት ዘመን ግሪኮች የአምልኮት ማዕከል በነበረው የዴልፊ ቤተ መቅደስ ግድግዳ ላይም ተጽፎ እንደ ነበር ተመዝግቦአል:: የዕውቀትን አስፈላጊነት የሚያስቀድም የሚያጠናክር ነው:: ሰው አውቆ ወዶ ክፋትን አይሠራም” ፕላቶን ባዮች ነበሩ:: የሚለውን መፈክር የዕለት ተግባር መመሪያ በማድረግ በአደባባይ፣ በገበያ፣ በየመንገዱ ሳይቀር ሰው በሚገኝበት ቦታ ሁሉ በጥያቄ መልስ ዲያሎጎስ ሰውን በገዛ ጥረቱ እስከ ሐሳቦቹ ጥንተ ልደት ድረስ በመመራመር እንዲደርስ ያስተምር ነበር:: ዝነኛው የማዋለድ ዘዴ (ሜዩቨቲኪ) የተባለው የሚጠቀሰው እዚህ ላይ ነው:: በባሕሪያችን ውስጥ በአምሳለ ዘር የተቀመጡ ጥንተ ነገሮች አሉ:: እነሱን ፈልጎ ማግኘት፣ ማዳበር የትምህርት ዓላማ፣ የዕውቀት የጥረት መድረሻ፣ የምግባር የሥነ ምግባር መሠረት ነው:: ይህ ከሌለ እንደ ዕውር በዳበሳ መጓዝ ይሆናል:: ፕላቶን የሚባለው ተማሪው ይህንን ትምህርትና የማስተማር ዘዴ ዕድሜውን ሙሉ በመድከም የረቀቀ ጥበብ በተመላው ሥነ ጽሑፍ ቀርጾ ለዘለቄታው አኑሮለታል::

ስለ ሰውነት የሚያስብ፣ የሚሰጋ ሁሉ በዚያ መንገድ እንዲያልፍ የሚመክሩ ጥቂቶች አይደሉም:: ብዙ ነገር የሚረግፍለት ስለሆነ ምክሩን ከመደገፍ የማንቆጠብ መሆናችንን እየገለጽን፤ ሶክራቲስ በሐሰት ተከሶ በሀገሩ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሞት ቅጣት ከመቀበሉ በፊት ተግባሩን፣ ሥነ ምግባሩን በመከላከል (አፖሎጊያ) ከተናገረው ባጭሩ እንጠቅሳለን:: ስለ ነፍስ ማሰብ መጠንቀቅ (ኤፒሜሊያ

ፕስሂስ) እንደሚገባ በተነገረው ላይ እናተኩራለን::

“አቴናውያን ወገኖቼ ሆይ! ምንም እንኳ ብወዳችሁና ባከብራችሁ ከእናንተ ይልቅ ለሰማይ መታዘዝን እመርጣለሁ:: እስከ መጨረሻው ጥበብን ከመከታተል አላቋርጥም:: እንዲሁም በመንገድ ለምትገጥሙኝ ሁሉ እውነትን ከመጠቆምና ከማሳሰብ ቸል አልልም:: እንደ ልማዴ እንዲህ እያልኩ:: መልካም ወዳጄ ሆይ! በጥበባት ሀብት ዝነኛ የሆነችው የታላቋ ከተማ የአቴና ዜጋ ነህ:: ብልጽግናን፣ ክብርን፣ ዝናን፣ የመሰሉትንም ሁሉ ለማከማቸት ይህን ያህል ስትደክም ለጥበብ፣ ለዕውቀት ለነፍስህ መሻሻል ምንም አለማሰብህ አያሳፍርህምን ለነዚህ ነገሮች የሚያስብ መሆኑን በመግለጽ ቢቃወመኝ ወዲያው ትቼው መንገዴን አልቀጥልም:: እጠይቀዋለሁ:: እፈትሸዋለሁ:: የሚወደውን በጎነት (አሬቲ) እንደሚለው ያልያዙ ሆኖ ካገኘሁት እጅግ ውድ የሆኑትን ነገሮች ርካሽ አድርጎ፤ ዋጋ ቢስ የሆኑትን ውድ አድርጎ በመቀበሉ ሳልወቅሰው አላልፍም:: ለሚገጥመኝ ሁሉ ሽማግሌም ሆነ ወጣት፤ በተለይም፣ ወገኖቼ፣ ሕዝቤ ለሆናችሁ ለእናንተ ይህን ከማድረግ አልቆጠብም:: ይህ የግዜር ትእዛዝ ነው:: አትጠራጠሩ:: እኔ ለዚህ አገልግሎት ከመቆሜ የተሻለ ሌላ ዕድል አቴናውያን እንዳልገጠማችሁ አምናለሁ:: እናንተን ከመምከር በስተቀር ሌላ ሥራ የለኝም:: ወጣትም፣ ሽማግሌም ለአካላችሁ፣ ለሀብት ለንብረት ከምታስቡት የበለጠ ለነፍሳችሁ መሻሻል አስቡ:: ለዚህኛው ቅድሚያ ስጡ:: ደግነት ከሀብት የሚገኝ አይደለም:: ሀብትንና ማናቸውንም ሌላ ነገር ሁሉ በግልም በማኅበራዊም ኑሮ ረገድ ለሰው ዋጋማ የሚያደርገው ደግነት ነው:: ይህን በመናገሬ ወጣቶችን አሳስተሃል ትሉኝ እንደሆነ ግድ የለኝም::

እጓለ ገብረ ዮሐንስ “ብፁዓን ንጹሐነ ልብ” (2005)

ለአገሬ እዘኑላት ለሦስት ሺህ ዓመታት

ልጆች ወልዳ… ወልዳ…

ልጆች ወልዳ… ወልዳ…

ልጆች የሞቱላት…. ልጆች የሞቱባት…

ትልቋን አገሬን፣ ትልቋን ምስጢሬን

በጉባኤ ጥሯት፣ በሱባኤ ጥሯት

ጥሩና ጠይቋት፣ ጥሩና መርምሯት

ከምድሯ ውስጥ ግፍን፣ ከደጆቿ ሀፍረትን

ጠራርጎ የሚያጠፋው፣ በአመድ ፋንታ አክሊልን

የሚያጎናፅፈው መሲሁ የት አለ?

ብላችሁ ጠይቋት፣ ብላችሁ መርምሯት

ቅጥሮቿን በፅኑ የሚገነባቸው

እጆቿን ከእሥራት የሚያላቅቃቸው

የት ሄዷል? ብላችሁ ሀገሬን ጠይቋት

ዝም ካለቻችሁ፣ መልሷን ካልሰማችሁ

መለከት ነፍታችሁ፣ ጉባኤ ጠርታችሁ

ለሀገሬ እዘኑላት፣ በሀገሬ እዘኑባት

ለሦስት ሺህ ዓመታት

ወልዳ… ወልዳ… ወልዳ…

ልጆች ለሞቱላት… ልጆች ለሞቱባት…

አረጋ ኃ/ሚካኤል “ሰው መሆን ይሻላል” (2005)

በታሪክ ውስጥ ህይወታቸው ከሚመስጡኝ ሰዎች መሃል ማህተመ ጋንዲ አንዱ ነው:: ጋንዲ እንግሊዞችን ፍጹም ሰላማዊ በሆነና ለእነርሱ ጨርሶ ሊገባቸው በማይችል እምነትና መንገድ የታገላቸው ነው:: ከምዕተ ዓመታት ቅኝ ግዛታቸው ለማስወጣት የህንድን ህዝብ እያንቀሳቀሰ ስለሚፈታተናቸው ብዙ ጊዜ እስር ቤት ይከቱት ነበር::

ታዲያ ወደ መጨረሻው አስከፊ እስር ቤት በወረወሩበት ጊዜ ምን ይላቸዋል መሰለህ? “እናንተ አውሮፓውያን ወዳጆቼ ሆይ! የሰው ልጅ እኮ በአራት ግድግዳ የሚታሰር ግኡዝ ነገር አለዚያም እንሰሳ አይደለም:: የሰው ልጅ መንፈስ ነው:: እዚህ በእስር ሳለሁ ጽናቱን እምነቴ ህንዳውያን ወገኖቼን ያንቀሳቅሳል” ይላቸዋል:: “እስር ቤት ክፉ የሚሆነው በመንፈስ ለታሰሩና በግድግዳ ለሚወሰኑ እውነተኞቹ እስረኞች እንጂ መንፈሳቸውን ከፍርሃትና ከጥላቻ ነጻ ላወጡ መንፈሳውያን እስራት አያስጨንቃቸውም፤ አያሸብራቸውም” ይላቸዋል::

አንድ ጊዜ ደግሞ ጋንዲን የመጨረሻዎቹ ዱርዬዎችና ነፍሰ ገዳዮች መካከል ይከቱታል:: ጋንዲ ወደዚያ ሲገባ “እነሆ ወንድሞቼ መሃል ገባሁ:: ከዛሬ ጀምሮ የዚህ ቤተሰብ አካል ነኝ” ነው የሚለው:: ሐዘን ቢሰማው እንኳ ሐዘኑን በተስፋና በፍቅር ሊታገለው ይጀምራል እንጂ ቅሬታና ማጉረምረምን አያሰማም:: በእነዚህ የማይጠቅሙ ተብለው በተጣሉ ዱርዬዎች ውስጥ ፍቅርና መልካምነት እንዳሉ ያውቃል ብቻ ሳይሆን ያምናል:: እናም ኃላፊነት ይወስዳል:: የእስር ቤቱን ቆሻሻ ማጽዳት ይጀምራል:: እነዚያን አይጠቅሙም

እንደውም ማኅበራዊ አደጋ ናቸው ተብለው የተጣሉ ነፍሰ ገዳዮችን በማክበር አክብሮት ከማሰጠው መልካም ስሜት ያስተዋውቃቸዋል:: ከእግዚአብሔር ያስተዋውቃቸዋል:: ጤና አጠባበቅን፣ አብሮ መኖርን ያስተምራቸዋል:: ታሪክ የማያውቁትን ታሪክ፣ ማይማኑን ማንበብ መፃፍ ያስተምራቸዋል:: እንዲህ በመልካም ተግባር ተጠምዶ ሲውል ስለ እስር የሚያስብበት ጊዜ አልነበረውም:: እንግዲህ ስለ ነጻነታቸው ሲል የራሱን ነጻነት ያጣላቸው ህንዳውያን ማለት እነዚህን ወህኒ የተጣሉትንም እንደሚጨምር ያውቃል:: እናም የብርሃን ተስፋውን በወህኒ ጨለማ ውስጥ ሳለ ይበልጡኑ ጸንቶና አምኖ እየታገለለት ነው ማለት ነው::

የትግሉ መንገድ ግን ጥላቻን በጥላቻ ማሸነፍ እንደማይቻል ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ጥላቻን በፍቅር መፈተን ነው:: ስለዚህ መታሰሩ አስጨንቆ አላማውን ጥሎ እጁን እንዲሰጥ አያስገድደውም:: ይልቁንም በዚያ ጨለማ ውስስጥ ህይወትን ይጀምራል:: እናም መታሰሩን ይረሳዋል ልበልህ:: በዚህ ጊዜ እነሱው አሳሪዎቹ ራሳቸው አስታውሰው ነው የሚፈቱት:: “የረገጥኳትን መሬት ለመባረክ ሥልጣን ተሰጥቶኛል” ነው የሚለው::

እና ወንድሜ! ማህተመ ጋንዲ በዚህ የህይወት መንገዱ ያስተማረኝ ትልቅ እውነት “በዙሪያህ የሚታይህን ክፋት መቋቋም ካቃተህ ‘እኔን ምን ነካኝ?’ እንጂ ‘ዓለም ምን ነካት?’ ብለህ አትጠይቅ” የሚል ትምህርት ነው:: እንዲህ ብለህ ብትጠይቅም መልስ አታገኝም:: ዓለም ክፉ ናት ብትል ራስህ ክፉ ናት ካልካት

ከዓለም በእጥሩ የከፋህ ትሆናለህ:: በምትጠላው ነገር ውስጥ ያለውን መልካም ነገር የምታስተውልበት ዓይኖች ቢኖሩህ ክፉውን መልካም ታደርገዋለህ:: እርሱን ፈውሰህ አንተም ትፈወሳለህ::” ማህተመ ጋንዲ በዚህ ባህሪው ራሳቸው እንግሊዛውያኑ ቅኝ ግዢዎች፣ ሙስሊሙ፣ ክርስቲያኑ፣ የሌላ እምነት ተከታዮቹ ሳይቀሩ ይወዱት፤ ይከተሉትና ያምኑት ነበር:: እንግሊዞቹ ተብትበው በወጡት መከፋፈልና ጥላቻ ምክንያት በተፈጠረው እርስ በእርስ የመጠፋፋት ጦርነት ውስጥ ሙስሊሞቹ ሂንዱዎቹን እያባረሩ በቆንጨራ በሚጨፈጭፉ ሠዓት እንኳ ማህተመ ጋንዲን ግን ይሰሙት ነበር:: ይከተሉት ነበር፤ እርሱ ዘንድ ሲደርሱ በፍቅሩ ጭካኔያቸውንና ቂም በቀላቸውን አሸንፎ ያንበረክካቸው ነበር::

የሁሉንም እምነት መጻሕፍት አየገለጠ በየእለቱ ከሁሉም ህንዳውያን ጋር አብሯቸው ይጸልይ ነበር:: እናም ጋንዲ የቱንም መጥፎ የተባለን ቦታና ሃሳብ ወደ መልካም የመለወጥ ምሳሌ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል:: ስለዚህ በመሸ ጊዜ ንጋትን በማሰብ ተስፋህን አምነህ ጉዞህን ጀምር ማለቴ እንጂ የሁሉም ክፍ ነገር መጨረሻ በራሱ መልካም ነገርን ያመጣል ማለቴ አይደለም:: የክፉ ነገር መጨረሻማ ጥፋት ነው:: መልካሙን የሚያመጣው የኛ ጽናት ነው ማለቴ ነው:: በመጨረሻው ጨለማ ውስጥ ወደ ብርሃንህ ተመልከት ማለቴ ነው::

አርክቴክት ሚካኤል ሽፈራው “ፍልስምና” በተሰኘው መጽሐፍ ላይ ለቴዎድሮስ ተክለ አረጋይ ካወጋው

(2004)

ማህተመ ጋንዲ ብርሃነ ልቡና

ፎቶ በ

ሪፖርተ

ር/መስፍ

ን ሰሎ

ሞን

ኅዳር 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ በስተሰሜን አቅጣጫ በሚገኘው ዓባይ በረሃ መግቢያ ላይ የተገለበጠውን አይሱዙ ለማንሳት እንቅስቃሴ ሲደረግ

Page 42: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 42|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

የሚለውን ለማወቅ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል:: ግን በግርድፉ በተለይ ከሕገወጥ የዜጎች ዝውውር ጋር ተይይዞ በተለያዩ መድረኮች የሚሰጠው ትምህርታዊ ገለጻ፣ ክትትልና ቁጥጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለና መንግሥትም ችግሩን ለማስወገድ ጥረት እያደረገ ያለ ይመስለኛል:: በተቀናጀ መንገድ መሆኑ ላይ ግን ችግር መኖሩ ይታያል:: የሚመለከታቸውና ባለድርሻ አካላት ማለትም ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ኢሚግሬሽን፣ ፖሊስና ሌሎቹም በተገቢው መንገድ ተቀናጅተው የመሥራት ዕድሉ ጅምሩ እንዳለ እንሰማለን:: ነገር ግን እንደማኅበር ከእኛ ጋር ለመሥራት ዕውቅና ሰጥቶ ከእኛ ጋር የመንቀሳቀሱ ነገር ከሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በስተቀር ሌሎቹ እምብዛም ናቸው:: አይኤልኦ (የዓለም ሥራ ድርጅት) ብዙ እየረዳን ነውና ልናመሰግነው ይገባል:: ብዙ ጥረት ሲደረግ ይታያል:: ነገር ግን ከችግሩ ስፋትና ሥር የሰደደ ከመሆኑ አንፃር እየተወሰደ የሚገኘው ዕርምጃ እኩል ሊሄድ አልቻለም:: የዚህን ዘርፍ የሚከታተልና አስፈላጊው ነገር ሁሉ የሚያደርግ ራሱን የቻለ አንድ ኤጀንሲ ቢኖር የተሻለ እንደሚሆን እምነታችን ነው:: ብዙ ትኩረት ክትትል የሚፈልግ ጉዳይ ነው:: ብዙ ተቀባይ አገሮች ሠራተኞች ከሚያገኙባቸው አገሮች ጋር ጤናማ ግንኙነት የላቸውም:: በተለይ ከመብት መጣስ ጋር ተይይዞ:: በአሁኑ ጊዜ ብዙ አገሮች ወደ ኢትዮጵያ ትኩረት እያደረጉ ነው:: ይኽንን ገበያ በአግባቡ ለመምራት መንግሥት፣ ኤጀንሲዎችና እኛም እንደ ማኅበር ዝግጁ ልንሆን ይገባል:: ዝም ብለን የሰው ኃይል መላክ ብቻ ሳይሆን የምንልከው የሰው ኃይል ምርታማ እንዲሆን በማስተማር፣ ያለውን ነገር ሁሉ በማሳወቅ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ መሥራት አለብን:: የሚያገኙትን ገንዘብ እንዴት ማስተዳደር እንዳለባቸው፣ ቤተሰባቸውንና አገራቸውን በምን መልኩ መርዳት እንዳለባቸው ማሳወቅ ይገባናል::

ሪፖርተር፡- ማኅበራችሁ የማስፈጸም ኃላፊነቱ እስከምን ድረስ ነው?

አቶ መዝገቡ፡- ማኅበራት የሥልጣን ገደብ አላቸው፤ የትኛውም ማኅበር ያለው የማስፈጸም ሥልጣን በአባሎቹ ላይ ብቻ የተገደበ ነው:: ኤጀንሲዎቹ የማኅበሩን ሕገ ደንብና ሥነ ምግባር ተቀብለው እንዲሠሩ ማድረግ ነው:: ለዜጎች ተገቢውን አገልግሎት መስጠት ነው:: ከሚያገኙት የአገልግሎት ክፍያ ላይ ተገቢውን የመንግሥት ገቢ የመክፈል ግዴታ እንዳለባቸው ማሳወቅና መከታተል የማኅበሩ ኃላፊነት ነው:: በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ላይ እንዳይገኙ መምከርን፣ ሰላማዊ የሆነ ሥራ እንዲሠሩ ማስቻልም ኃላፊነቱ የማኅበሩ ነው:: ይኽንን የማይፈጽሙ አካላት ላይም ዕርምጃ የመውሰድ ሥልጣን አለው:: ሕገወጦችን ተሸክሞ የሚሄድ ማኅበር አይደለም:: በሥነ ምግባር ደንባችን መሠረት ዕርምጃ እንወስዳለን:: ለሚመለከተው የመንግሥት አካል በማሳወቅ እንደ ጥፋቱ መጠን በሕግ እንዲጠየቅም የማድረግ ኃላፊነት አለብን::

ሪፖርተር፡- በአሁኑ ጊዜ ምን ያህል ኤጀንሲዎች የማኅበሩ አባል ሆነዋል?

አቶ መዝገቡ፡- አባል የሆኑ ኤጀንሲዎች በቁጥር ብዙ ናቸው:: ነገር ግን አባል የሆኑበት መንገድን ስናጠናው ወደው ሳይሆን ማግኘት ያለባቸው ጥቅም እንዳለ በማመናቸው ነው:: ግን ሁሉም አይደሉም:: ለምሳሌ የዮርዳኖስን ሥራ በሚመለከት የተዋዋልነው፤ ሠራተኛ መቅጠር የሚፈልጉት በማኅበር ከተደራጁ ኤጀንሲዎች ጋር ብቻ ስለሆነ ወደ ዮርዳኖስ መላክ የሚፈልግ ኤጀንሲ የግድ የማኅበራችን አባል መሆን አለበት:: በሳዑዲ ያለው የሰው ኃይል ተቀባይ ማኅበር (ስናርኮም) ጋርም ተፈራርመናል:: ወደ ሳዑዲ ለመግባትም የእኛ አባል መሆን አለባቸው:: ሁሉም መመዝገብ እንዳለባቸው አምነው አባል ይሆናሉ:: ነገር ግን በአባልነታቸው የገቡትን ቃል የማይወጡ ኤጀንሲዎች አሉ:: ሕገወጥ ተግባር ላይ የተሰማሩ አሉ:: ስማቸውን በዝርዝር ለይተን አውቀናል:: ከሚመለከተውም የመንግሥት አካል ጋር እየተነጋገርንና ክትትል እያደረግን ነው:: ዕርምጃ እየተወሰደባቸውም ያሉ አሉ:: በጠቅላላ 300 አካባቢ ኤጀንሲዎች የማኅበሩ አባል ሆነዋል፤ ከአስር በላይ ተሰርዘዋል:: ከ40 በላይ የታገዱ አሉ:: ወርኃዊ ሪፖርት ባለማቅረባቸውም ከ80 በላይ በማስጠንቀቂያ ላይ እንዳሉ መረጃ አለን::

ሪፖርተር፡- ወደ ቀጣሪ አገሮች የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን አስፈላጊውን የሕክምና ምርመራ ለማድረግ እስከ 850 ብር እየከፈሉ ይገኛሉ:: ነገር ግን በአገር ውስጥ የተለያዩ ችግሮች እየደረሱባቸው የምርመራ ውጤቱን አግኝተው ከተጓዙ በኋላ በተቀባይ አገሮችም ችግር ይደርስባቸዋል:: ትክክለኛ የሕክምና ውጤት አይደለም ተብለውም የሚመለሱበት አጋጣሚ አለ:: ማኅበራችሁ በዚህ ዙሪያ ምን እየሠራ ነው?

አቶ መዝገቡ፡- ትክክል ነው ችግሮች አሉ:: ወደ ዓረብ አገሮች የሚሄዱ ዜጎች በዓረብ አገሮች በተመረጡ ጋምካ በሚባል የጽሕፈት አገልግሎት በሚሰጥ ድርጅት የተመረጡ ስምንት የሚደርሱ የሕክምና ተቋማት አሉ:: በእነሱ አማካይነት ሕክምና ለማግኘት ብዙ ችግር መኖሩ ይታወቃል:: ተቋማቱ ያሉት በተወሰነ አካባቢ ብቻ ነው:: አዲስ አበባ ስላሉ ከክፍለ ሀገር የሚመጡ ዜጎች ካለው የሕዝብ ብዛት አንጻር ብዙ እንግልት እየደረሰባቸው መሆኑ ይታወቃል:: ብዙ ሰልፍ ይታያል፣ ተጓዡም የማይጓዘውም ተሰላፊ ይሆንና ብዙ ችግሮች ሲፈጸሙ ይስተዋላል:: ተመርምረው የሚሄዱት ዜጎች በሄዱበት አገር የመኖሪያ ፈቃድ ለማውጣት

በድጋሚ ይመረመራሉ:: በዚህ ጊዜ ከዚህ ብቁ ናቸው የተባሉት እዚያ ሲመረመሩ ብቁ የማይሆኑበት አጋጣሚ አለ:: ተጎጂዎች ለሥራ የሚሄዱት ብቻ ሳይሆኑ ኤጀንሲዎቹም ናቸው:: ምክንያቱም ልጆቹን ወደ መጡበት አካባቢ የመመለስ ግዴታ አለበት:: በሷ ምትክ ደግሞ በራሱ ወጭ ሌላ ሰው መልምሎ የመላክ ግዴታ አለበት:: አንድ ኤጀንሲ በቀላሉ ከአንድ ሺሕ ዶላር በላይ የሚከስርበት ሁኔታ ያጋጥመዋል:: በዚህ የተነሳ እኛ ከጋምካ ጋር በተደጋጋሚ ውይይት አድርገናል:: መግባባት ላይ ለመድረስ በሂደት ላይ ነን:: በምርመራ ምክንያት የሚመለሱ ወገኖችን ኪሳራ በምን መልኩ ማቻቻል እንደሚገባ እየተነጋገርን ነው:: የሄዱ ሁሉ በሕክምና ብቻ ይመለሳሉ ማለት አይቻልም:: ሌሎች የሚመለሱባቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉና:: እኛ ለመንግሥትም በግልጽ እያስረዳነው ያለነው የምናገኘው ኮሚሽን ሙሉ በሙሉ ቀረጥ ሊከፈልበት አይገባም የሚል ነው:: ታክስ ሊሆን የሚገባው ተለይቶ መቀመጥ አለበት:: ብዙ ያልተጠበቁ አደጋዎች ያጋጥሙናል:: የምናገኘው ጥቅም ውስን ነው በማለት ለኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ጭምር አሳውቀናል::

ሪፖርተር፡- ማኅበራችሁ ከተቀባይ አገሮች ጋር ያለው ግንኙነትም ምን ይመስላል? ከስንት አገሮች ጋርስ ግንኙነት አላችሁ?

አቶ መዝገቡ፡- እስካሁን በሕጋዊ ሁኔታ እየተገናኘን ያለነው ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመናል:: በአሁኑ ወቅትም የማኅበሩ ፕሬዚዳንት መጥተው ከኤጀንሲዎች ጋር ውይይት አድርገዋል:: በተለይ ዜጎች ሳዑዲ አረቢያ ከደረሱ በኋላ የሚደርስባቸውን ችግር እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል በስፋት ተወያይተናል:: ለችግሩ መፍትሔ እንደሚሰጡም ምላሽ ሰጥተውናል:: በቅርበት እየሠራን ነው:: በኩዌት ከሚገኘው አቻ ማኅበር ጋር ግንኙነት ለመፍጠርና ተመካክረን ለመሥራት ጥረት እያደረግን ነው:: ወደ ኩዌት ሄደን ለመወያየት በሠራተኛና ማኅበራ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል መሄድ የሚገባን ኃላፊዎች ስም ወደ ኩዌት ኤምባሲ ቢተላለፍም ኤምባሲው እንዳንሄድ ከልክሎናል:: በተለይ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኩዌት ተገኝተን በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር በአካል ተገኝተን እንድንመለከት አማራጮችን ለመንግሥት አጥንተን እንድናቀርብ እንዲያደርጉልን እየጠየቅን ነው:: ዜጎች እንዴት እየሠሩና በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ ለመመልከትና አላስፈላጊ በደል እየተፈጸመም ከሆነ ለማቆም የምንችለውን ሁሉ ለማድረግ እየተንቀሳቀስን ነው:: ሚኒስትሩ ትብብር እንዲደረግልን ለሥር ሠራተኞች ደብዳቤ መስጠታቸውን ብንሰማም ተቀባዩ ኃላፊ ግን ደብዳቤውን ሊሰጠን አልቻለም:: ለምን መያዝ እንደፈለገም ግልጽ አልሆነልንም:: በጣም ቅሬታ ገብቶናልና በቀጣይ ለሚመለከተው ሪፖርት እናደርጋለን:: ሌላው በቅርበት እየሠራን ያለነው ከዮርዳኖስ ማኅበር ጋር ነው:: ሥራ ባይጀመርም ከሌሎቹ ተቀባይ አገሮች ባገኘነው ልምድ ተጠቅምን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመናል:: ለመንግሥትም አሳውቀናል:: የምንልካቸውም ዜጎችም የሠለጠኑ እንደሚሆኑ የስምምነቱ አካል አድርገነዋል:: የሙያ ክህሎት የሌለው ዜጋ እንደማይሄድ ተስማምተናል:: መንግሥትም ተስማምቶበታል::

ሪፖርተር፡- ወደ ዱባይ ሠራተኞች እንዳይሄዱ እግድ ተጥሏል:: ምክንያቱ ምንድነው? በምንስ ሁኔታ ላይ ይገኛል?

አቶ መዝገቡ፡- ውስን የማኅበራችን አባላት የዱባይን ሥራ ይሠሩ ነበር:: ያጋጠሙ ችግሮች ስለነበሩ ለችግሮቹ መፍትሔ ለመስጠት ሲል መንግሥት ለጊዜው ማገዱን አስታውቋል:: ዱባይ ባለው ቆንስላ አማካይነት የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ችግሩን በመፍታት ሕጋዊ በሆነ መንገድ ዜጎች የሚሄዱበትን መንገድ እያመቻቹ መሆኑን ሰምተናል:: እንደ ማኅበር መቼ እንደሚከፈትና ወደ ሥራ እንደሚገባ መረጃው ለጊዜው የለንም:: ዋናው የተዘጋበት መንገድ ሕገወጦችን ለመከላከልና በዜጎች ላይ የሚደርሰውን ሞት፣ ስቃይና እንግልት ለማስቆም ነው::

ሪፖርተር፡- በሳዑዲ ዓረቢያ ያሉ የኢትዮጵያ ቆንስላዎች ወደ ሳዑዲ የሚላኩ ሠራተኞች ስለሚያገኙት ደመወዝ መወሰን የሚችሉት እነሱ እንደሆኑና እጅግ በወረደ ደመወዝ መቅጠር እንደሚቻል እየገለጹ ነው የሚባል መረጃ አለ:: ስለዚህ ጉዳይ ማኅበሩ የሚያውቀው ነገር አለ?

አቶ መዝገቡ፡- በኩዌትና በሳዑዲ ዓረቢያ የምንሰማቸው ነገሮች ጤናማ አይደሉም:: በተለይ ጅዳ ላይ እንደሰማነውና በደረሰን መረጃ መሠረት ኤምባሲው የሰው ኃይልን በርካሽ ዋጋ ሊያቀርብ እንደሚችል በአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ማስነገሩን ነው:: የሚመለከተው አካል ነገሩን አጣርቶ ተገቢ ነው አይደለም የሚለውን መወሰን የሚገባው ይመስለናል:: ተልዕኮአቸውና ኃላፊነታቸው አይደለም:: በጋዜጣ ላይ መውጣቱ መረጃው አለን:: በዚህ ጉዳይ የሚሳተፉ የኤምባሲ ሠራተኞች አሉ፣ በግል ደረጃ ሊጠየቁ ይገባል:: በኩዌት አካባቢም ከአሠሪዎቿ ጋር ባለመስማማት ወደ ኤምባሲ ለመጠለል ስትሄድ ኤምባሲው ውስጥ ባሉ ግለሰቦች አማካይነት ለሌላ አሠሪ እንደሚሸጧት ነው ያለን መረጃ የሚያመለክተው:: ይኽንን ለማጣራት ነበር ወደኩዌት መሄድ የፈለግነው:: ኤምባሲው ቪዛ ሲከለከክለን ጥርጣሬያችን እየበረታ ሄዷል::

ሪፖርተር፡- በኢትዮጵያ የኩዌት ኤምባሲን አነጋግራችኋል?

አቶ መዝገቡ፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያዩ

‹‹ወደ ዓረብ አገሮች... ከገጽ 15 የዞረ

ጊዜያት ደብዳቤ ቢጽፍልንም ሊቀበሉን አልቻሉም:: ይኽንንም አሳውቀናል:: አምባሳደሩን ጠርተው እስከማነጋገር እንደደረሱም መረጃዎች አሉን:: እስካሁን አልተሳካልንም:: ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ጋር ሆነን ትግሉን እንቀጥላለን:: በግለሰብ ደረጃ መሄድ እንችላለን:: የምንሄደው ለዜጎች ጉዳይ በመሆኑ ከመንግሥት እውቅና ተሰጥቶን ሄደን መሥራት ስለምንፈልግ ብቻ ነው ኤምባሲውን እየጠየቅን ያለነው:: ግን እንዳንሄድ የሚፈልጉ ኃይሎች እያስተጓጎሉብን ነው:: የዜጎች ጉዳይ ነውና ዝም ብለን አንቀመጥም:: መንግሥትም ይረዳናል የሚል እምነት አለን::

ሪፖርተር፡- ከሌሎቹ አገሮች ማኅበራት ጋር ያላችሁ ግንኙነትስ ምን ይመስላል?

አቶ መዝገቡ፡- በተለይ ከሳዑዲ ዓረቢያ አገር ማኅበራት ጋር ጥሩ ግንኙነት አለን:: በኢትዮጵያ የሳዑዲ ዓረቢያ ኤምባሲ ቆንስላ በፍፁም ቅንነት ከማኅበራችን ጋር ተባብረው እየሠሩ ናቸው:: ችግሮች ቢኖሩም ለመፍታት ከማኅበራችን ጋር ጥረት ያደርጋሉ ያማክሩናል:: በኤጄንሲዎች ላይ ያሉትን ችግሮች በመንቀስ እንዲያስተካክሉ ቀድመው ይነግሩናል:: እኛም የምንችለውን ሁሉ ለማድረግ እየሠራን ነው:: ነገር ግን በኤምባሲው ውስጥ ቅንነት የጎደለው ሥራ የሚሠሩ አሉ:: በተለይ በጥበቃ ላይ የተሰማሩ የሳዑዲ ዓረቢያ ዜግነት ያላቸውና ኢትዮጵያውያንም በዜጎቻችን ላይ ክብራቸውን ጭምር የሚነካ ተግባር የሚፈጽሙ አሉ:: በተደጋጋሚ ለአምባሳደሩም አሳውቀናል:: ችግሮቹን በመነጋገር የመፍታት ዕድላችን ግን ሰፊ ነው:: በተለይ ቆንስላው የሚያደርጉት ትብብር እጅግ በጣም የሚያስመሰግናቸው ነውና ሌሎችም የእሳቸውን አርአያ ቢከተሉልን የተሻለ መሆኑን መናገር እንፈልጋለን::

ሪፖርተር፡- በአሁኑ ጊዜ በየቀኑ ምን ያህል ዜጎች ለሥራ ወደ ዓረብ አገሮች ይሄዳሉ?

አቶ መዝገቡ፡- በአሁኑም ጊዜ ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ በቀን ከአንድ ሺሕ እስከ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ይሄዳሉ:: ባለፉት ሁለት ወራት ግን ይኽ አሐዝ ሊቀንስ ይችላል ብዬ አስባለሁ:: ምክንያቱም ከረመዳን ወር በኋላ እየቀነሰ ይመጣና እንደገና እየጨመረ ይሄዳል:: ተቀባይ አገሮች ከሌሎች ሠራተኛ አቅራቢ አገሮች ጋር ያላቸው ግንኙነት ጥሩ ስላልሆነ ፊታቸውን ወደ ኢትዮጵያ በማዞራቸው የሠራተኞች ተፈላጊነት እየበዛ ይመጣል:: በዚህ መሠረት በቀጣይ ቁጥሩ ይጨምራል:: ሌሎች አገሮች የዜጎቻችን መብት ካልተከበረ አንልክም በማለታቸው ከፊሊፒንስ፣ ከሕንድና ሌሎች አገሮች ጋር ያላቸው ግንኙነት እያቆመ ነው:: ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር ባደረግነው ንግግር ማለት ከማኅበራት ጋር፣ ኤጀንስ ከኤጀንሲ ጋር በሚያደርገው ግንኙነት የሚላኩ ሠራተኞች ተቀባይነት እንደማይኖራቸውና ሁሉም የቅጥር ሁኔታ በማኅበራት ሥር እንዲሆን ኩባንያ አቋቁመዋል:: ኩባንያው ሠራተኞችን ወስዶ በኤቲኤም ማሽን አማካይነት አካውንት ከፍቶላቸው ደመወዛቸውን በየወሩ እዚያ እንዲወስዱ፣ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በስልክ እንዲነጋገሩ ቀፎ ይዘው እንዲሄዱ ተደርጎ እንደደረሱ ከኢትዮጵያ 100 ብር ተሰጥቷቸው እንዲገናኙ ይደረጋል:: ኩባንያው በሚመድባቸው የሥራ ቦታ እንዲሠሩ ይደረጋል::

ሪፖርተር፡- ሠራተኞቹ ሲላኩ የሚከፈላቸው ውስን ክፍያ

ስንት ነው?

አቶ መዝገቡ፡- ዝቅተኛው 180 ዶላር ነው::

ሠልጥነው ቢሄዱ ግን የተሻለ ክፍያ ይከፈላቸዋል::

ተቀባይ አገሮችም ቃል ገብተውልናል::

ሪፖርተር፡- በውጭ አገሮች ማለት ወደ አረብ አገሮች በቤት ሠራተኛነት በሚሄዱ ዜጎች ላይ የሚደርሰው ሞት፣ ስቃይና እንግልት ለማስወገድ ምን መደረግ አለበት ይላሉ?

አቶ መዝገቡ፡- በመጀመሪያ ደረጃ መንግሥት ዜጎች በአገር ውስጥ ሥራ የሚያገኙበትን መንገድ እንዲያመቻቹ እመክራለሁ:: ከዚህ ባሻገር ግን የተሻለ የሥራ አማራጭ ያጡ ዜጎች ደግሞ ሕጉን ተከትለው በሕጋዊ መንገድ ወጥተው እንዲሠሩ ዋናውና ትኩረት የምሰጥበት ምክሬ ነው:: ይኽን ለማድረግ ግን በውጭ ሥራ ስምሪት የተሰማሩ ሕገወጦችን ማለትም ደላሎች ከመስመሩ ወጥተው ወደሕጋዊ መስመር እንዲገቡ ወይም መንግሥት እንዲያስወግዳቸውና የዜጎችን ደህንነት መጠበቅ አለበት እላለሁ:: ይኽ ደግሞ ለታችኛው የወረዳ ኃላፊዎች እስከላይኛው ድረስ ያሉ ኃላፊዎች ትኩረት መስጠት አለባቸው:: በተቀባይ አገሮች የሚመደቡ ቆንስላዎችም የተሻለ ዕውቀት ያላቸው:: የሚመደቡበትን አገር ቋንቋ የሚያውቁ ቢሆኑና ስለዜጎች ተቆርቋሪ የሆኑ ቢሆኑ የተሻለ ለውጥ ይመጣል እላለሁ:: ማኅበራችን በማንኛውም ሠራተኛ ተቀባይ አገሮች ባሉ ኤምባሲዎቻችን አስፈላጊ ከሆነና መንግሥት አቅርቦ ካማከረን ተጨማሪ የሰው ኃይል ለመቅጠርም እንችላለን:: በአጠቃላይ በተቀናጀ መንገድ ብንሠራ በዘርፉ ላይ ያለውንና የሚያመነጨውን ኢኮኖሚ አገሪቱ በአግባቡ ልትጠቀም የምትችልበትን መንገድ ልናመቻች እንችላለን:: በዘርፉ ላይ ያለውን አጠቃላይ መረጃ ለኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዝርዝር መረጃ ሰጥተናል:: ምላሽ ግን አላገኘንም:: የታክስ ሥርዓቱን ተከትለን የሚፈለግብንን ሁሉ ለመክፈል እንድንችል፣ እንዲያወያየን፣ ያሉብንን ችግሮችና መልካም አሠራሮች ለይተን ተባብረን ለመሥራት አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጠን በዚህ አጋጣሚ መግለጽ እንፈልጋለን:: በተለይ ከታክስ ሥርዓቱ ጋር የሚሄድ አሠራር እንድንይዝና ኤጀንሲዎች ከሚደርስባቸው ውጣ ውረድ ሊድኑ ይችላሉና ባለሥልጣኑ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጠን በድጋሚ እንጠይቃለን::

እንደሚያወሩ እያጉተመተሙ። ‹‹እንዴት?›› አላቸው አጠገባቸው ያለ ወጣት። ‹‹በእውነት ዕድለኞች ናችሁ። ሰሞኑን የብሔር ብሔረሰቦች በዓል ሲከበር ይህንኑ ሳስብ ነበር። አይምሰላችሁ አገራችሁ እንዲህ እንደምታዩዋት አልነበረም የኖረችው። እውነቴን ነው ውሸት ምን ያደርጋል? እሱ መድኃኒያለም የደም ዘመኑዋን ቆጥሮ በመቻቻልና በፍቅር አጠባት። አይ ሰው! መቼም ከሰነበተ ብዙ ያያል። ምናለ እኔንም እንደናንተ አድርጎኝ ክፉውን ሳላይ በኖርኩ? አሁንም ክፉ አጠገባችሁ አይድረስ፤›› ሲሉ ምርቃቱን አሜን ብለን ተቀበልን። አዛውንቱ ሳይጨርሱ ቆንጂትና ደፋሩ ወጣት፣ ‹‹ወራጅ አለ›› ብለው ልክ እንደ ዘመናት ፍቅረኞች ተያይዘው መሀል መንገድ ላይ ወረዱ። ‹‹ወይ የአንዳንዱ ጮሌ ቴክኒክና ታክቲክ?›› ሲሉ አዛውንቱ የድሮ አራድነታቸው ፊታቸውን በትዝታ አበራው፡፡ ቴክኒክና ታክቲክ ለኳስ ብቻ ነው ያለው ማን ነው?

ወደ መዳረሻችን እየተቃረብን መጥተናል። ዕቅዳችን አልሆን ብሎ ነው እንጂ ጎዳናው ብዙ ያስኬደን ነበር። ‹‹ሰው እንዳሰበው መቼ ይጓዛል?›› ሲሉ አዛውንቱ አንዳንዶች ባልፈለጉት አቅጣጫ የመጡ ይመስላል። ውጥኑ ባጭር የቀረና የጀመረው እንዳይሆን ሆኖ የሚቀረው በሕይወት ሠልፍ ውስጥ ብዙ ነው። በዚያው ልክ እንዳሰበው የሚጓዝም ሳይረሳ። ‹‹ሞትን ክሰሰው ብባል የአገሬን መጨረሻ ሳያሳየኝ ሊወስደኝ መጠጋቱን አሳብቤ ፍርድ ቤት እገትረው ነበር፤›› ይላሉ ሌላ አዛውንት ደረቅ ሳል እያሳሉ። ‹‹አይዘዎት ኢትዮጵያችንን ጥለን አንጥላትም፤›› ቢል ወያላው ተስቶት አዛውንቱ ደግሞ፣ ‹‹እርፍ! ጭራሽ ስለመውደቅ ታወራኝ አንተ?›› አሉት ኮስተር ብለው። ሌሎቻችን ፈገግ ብለን ስናያቸው እያዩ፣ ‹‹ነገም ሌላ ቀን ነው ልጆቼ። በጭራሽ አሁን በምትሆኑትና

ባላችሁበት ሥፍራ ራሳችሁን እያያችሁ አትቁሙ፤›› እያሉ ሳላቸው መጣባቸው። ‹‹አገርን ትውልድ ነው የሚቀባበላት። በትውልድ ቅብብል ውስጥ የማይተነበየው ቀን ብቻ ነው። እንዳፋችን አድርጎት ማየት የምንፈልገው አገራችን ታላቅ ስትሆን ነው። ምን ዋጋ አለው ሞት የሚባል ክፉ ባይኖር ነበራ! ሆኖም እኛ ብናልፍ ዓይናችሁ ዓይናችን፣ እስትንፋሳችሁ እስትፋሳችን ነው፤›› ሲሉን ወኔ በልባችን ሲቀጣጠል ታወቀኝ። እንዲህ ዓይነቱ አጋጣሚ ሲፈጠር ውስጤ በሞራል ይገነባል፡፡ እንደ እሳት ይሞቃል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ በረዶ የጎረሱ ይመስል ስሜትም አይሰጣቸው፡፡ ልባቸው ያለው የግል ጥቅም ላይ ነዋ!

ታክሲያችን ወደ ካዛንቺስ ስትቃረብ የአንዱ ተሳፋሪ ስልክ ጮኸ፡፡ ‹‹ደርሻለሁ! ጠብቀኝ ደርሻለሁ!›› አለ፡፡ የቸኮለ ጠባቂና የዘገየ ተጠባቂ በየደረስንበት በሞባይል ሲጯጯሁ መስማት የተለመደ ነው፡፡ ‹‹ኧረ እባክህ ይኼው ሲኒማ ኢትዮጵያ ደርሻለሁ እኮ! በቃ ጠብቀኝ፤›› ሲል ሁላችንም ዞረን በመገረም አየነው፡፡ ካዛንቺስ ውስጥ ሆኖ ፒያሳ ነው ያለሁት ሲል አስገረመን፡፡ ‹‹ለነገሩ ‘የቸገረው እርጉዝ ያገባል’ አይደል የሚባለው? ቢቸግረው እኮ ነው አሥራ ሁለት ሰዎች መሀል ሆኖ የሚዋሸው፤›› አለኝ ከፊቴ የተመቀመጠ ጎልማሳ፡፡ አንዲት እናት ግን፣ ‹‹የለም! የለም! እንዲህ ዓይነቱ ውሸት ብሔራዊ ሆኖ በየቦታው ተለምዷል፤›› አሉ፡፡ ሴትየዋ ሁላችንንም በተራ እያዩ፣ ‹‹አይደለም እንዴ? ስንቶቻችን ነን በየቦታው ስንዋሽ የምንውለው? ከመንግሥት ሹም ጀምሮ እስከ ሊስትሮ ድረስ ስንቀደድ አይደለም እንዴ መሽቶ የሚነጋው? ብሔራዊ ውሸት በዛ…›› እያሉ ሲናገሩ ወያላው ‹‹መጨረሻ›› ብሎ ገላገለን፡፡ መልካም ጉዞ!

ብሔራዊ... ከገጽ 16 የዞረ

Page 43: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

|ገጽ 43 | ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

www.ethiopianreporter.com

ስ ፖ ር ት ስ ፖ ር ት

በደረጀ ጠገናው

ከሐምሌ 26 እስከ ነሐሴ 12 ቀን 2004 ዓ.ም. ድረስ በተካሔደው 30ኛው የለንደን ኦሊምፒክ ተሳታፊ ለነበረው የኢትዮጵያ ልዑክ ቃል ከተገባው 46 ሚሊዮን ብር ገቢ ያልተደረገ ገንዘብ እንዳለ ተገለፀ:: ገንዘቡን ለመስጠት ቃል ከገቡ ተቋማት አንዳንዶቹ በወቅቱ በልዑካን ቡድኑ ዙርያ ከስፖርት ቤተሰቡ ይቀርቡ ለነበሩ ቅሬታዎች ከሚመለከተው መንግሥታዊ አካል ማብራርያ የጠየቁ ስለመኖራቸው የሚናገሩ አሉ::

የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በአራት ዓመት አንድ ጊዜ በሚያከናውነው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች፣ ኢትዮጵያ ከ1949 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ1956) ጀምሮ በአትሌቲክስና ብስክሌት መሳተፍ ስትጀምር፣ ቦክስንም አካትታ ስትቀጥል በውጤት ደረጃ የቀናት ረዥም ሩጫው ብቻ ነው:: ነገር ግን ብስክሌትና ቦክስ በጀመሩት መቀጠል ሲሳናቸው በአትሌቲክሱ ግን ዛሬም ተሳትፎዋን አጠናክራ ትገኛለች::

የስፖርት ቤተሰቡና መንግሥት በየአራት ዓመቱ በሚከናወነው የኦሊምፒክ ጨዋታ ላይ ለሚሳተፉ ብሔራዊ አትሌቶች የሚጠየቁትን ሁሉ ሲያሟሉ ቆይተዋል::

ባሳለፍነው ክረምት በተከናወነው የለንደን 2012 ኦሊምፒክ ለተሳተፈውም ብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድን እንደተለመደው ሁሉ ሕዝብና መንግሥት በተጨማሪም ድርጅቶችና ግለሰቦች 46 ሚሊዮን ብር ቃል መግባታቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው::

ይሁንና በወቅቱ ቃል የተገባው ገንዘብ እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ገቢ እንዳልሆነ፣ እንዲያውም ቃል ከገቡት መንግሥታዊም ሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ የግል ድርጅቶች ውስጥ ከአንዳንድ ክልሎች በስተቀር ብዙዎቹ ማብራርያዎች የሚያስፈልጓቸው አሰራሮችን በመጥቀስ ክፍያውን ለመፈፀም የተቆጠቡ እንዳሉ የሚናገሩ አሉ::

እንደ ምንጮቹ በአዲስ አበባ ሒልተን ባለፈው ሐምሌ መጀመርያ አካባቢ በተከናወነው ፕሮግራም ለብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድኑ ቃል የተገባው ገንዘብ

የደቡብ አፍሪካ የአፍሪካ ዋንጫ በይፋ ሊጀመር 39 ቀናት ቀርተውታል:: ከ31 ዓመታት በኋላ መድረኩን የተቀላቀለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ባለፈው ቅዳሜ ዝግጅቱን ጀምሯል:: በኢንተር ኮንትኔታል ሆቴል ተቀምጦ መደበኛ ዝግጅቱን የጀመረው የአሰልጣኝ ሰውነት ቡድን፣ ከስዊድን የሱፍ ፍላህ፣ ከጀርመን ደግሞ ዴቪድ በሻህና ለግብፅ ዋዲ ዳግላ ክለብ እየተጫወተ የሚገኘውን ሳላዲን ሠይድንና ከአገር ውስጥ ክለቦች 23 ተጫዋቾችን በስብስቡ አካቷል:: ብሔራዊ ቡድኑ እስካሁን ባለው ጊዜ ቃል የተገቡለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን ባያደርግም፤ ነገር ግን በማይቀረው የ2013ቱ የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመርያ ጨዋታውን ጥር 13 ቀን 2005 ዓ.ም. ከዛምቢያ አቻው ጋር ይጫወታል::

ዛምቢያ የ2012 የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን መሆኗ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለ2013ቱ ተሳትፎዋ ከወዲሁ እያደረገች ያለው ዝግጅት በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ ሥጋት ፈጥሯል:: ምክንያቱ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እንደነዛምቢያም ባይሆን በዝግጀት መሐል አቋሙን የሚለካበት አንድ ወይም ሁለት ጠንካራ የወዳጅነት ጨዋታዎችን ማድረግ ሲገባው ሳያደርግ ዛሬ ላይ መድረሱ ለሥጋቱ ምክንያት እየሆነ ይገኛል::

በኡጋንዳ አስተናጋጅነት የተከናወነው የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገሮች (ሴካፋ) የእግር ኳስ ዋንጫ

ባሳለፍነው ሳምንት ተጠናቋል:: በሻምፒዮናው የተሳተፈው የኢትዮጵያ ሁለተኛ ቡድን ወደ ስፍራው ሲያመራ ታሳቢ አድርጎ የነበረው ለዋናው ቡድን መጋቢ የሚሆኑ ተጫዋቾች ይገኛሉ የሚል ነው:: ይሁንና ከቅዱስ ጊዮርጊሱ ያሬድ ዝናቡ በስተቀር ቡድኑ ይኼ ነው የሚባል እንቅስቃሴ

ማሳየት አለመቻሉም ተስተውሏል:: ይኼ መሆኑ ካልቀረ ደግሞ ዋናው ቡድን ሔዶ አጋጣሚውን ቢጠቀም የተሻለ ይሆን እንደነበርም የስፖርት ቤተሰቡ እምነት ሆኗል::

ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት በኢንተር ኮንትኔታል ሆቴል ተቀምጦ ዝግጅቱን እያከናወነ የሚገኘው የአሰልጣኝ ሰውነት ቡድን፣ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ ከማምራቱ በፊት የወዳጅነት ጨዋታዎችን እንዲያደርግ በዕቅድ ደረጃ ከተያዙት ጨዋታዎችና አገሮች የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገሮች (ሴካፋ) አካል የሆነችው ታንዛኒያ ትጠቀሳለች:: ይኸውም የአሰልጣኝ ሰውነትን የ“አይመጥኑንም” የቀድሞ አቋም ለትችት እንዲጋለጥ አድርጎታል::

የአሰልጣኝ ሰውነት ስብስቡ በረኞች ጀማል ጣሰው ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሲሳይ ባንጫ ከደደቢት፣ ዘሪሁን ታደሰ ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ደረጀ ዓለሙ ከሰበታ ከነማ፣ እንዲሁም ተከላካዮች ደጉ ደበበ፣ ቢያድግልኝ ኤልያስ፣ አበባው ቡጣቆና አሉላ ግርማ አራቱም ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ አይናለም ኃይሉ፣ ብርሃኑ ቦጋለ፣ ሥዩም ተስፋዬና አክሊሉ አየነው ከደደቢት ሲሆኑ፣ አማካዮች አሥራት መገርሳ ከመብራት፣ አዲስ ሕንፃ ከደደቢት፣ ዳዊት እስጢፋኖስ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ያሬድ ዝናቡና ሽመልስ በቀለ ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ሙሉዓለም መስፍን አርባ ምንጭ እና ፍፁም ተፈሪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አጥቂዎች አዳነ ግርማ፣ ኡመድ ኡክሪና ፍፁም

ገብረ ማርያም ሦስቱም ከቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ጌታነህ ከበደ ከደደቢት፣ እንዲሁም ሳላዲን ሰይድ ከግብፅ ዋዲ ዳግላ፣ በተጨማሪም የሱፍ ሳላህ ከስዊድን ግራ ተመላላሽ፣ ዴቪድ በሻህ አማካይ ተከላካይ ከጀርመን ሁለተኛ ዲቪዚዮን መሆናቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ነገር ግን ምርጫ ላይ ቅሬታ ያላቸው አሉ:: ለዚህም አሰልጣኙም ሆኑ የፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ክፍል ቀደም ሲል የገለፁት ምርጫው በነባርነት ሳይሆን በወቅታዊ ብቃት ላይ የተመሠረተ እንደሚሆን ነበር:: ይሁንና ወቅታዊ ብቃትን ታሳቢ ያደረገ ምርጫ ነው ብሎ ለማለት እንደሚቸገሩ ጭምር ያስረዳሉ::

ምክንያቱም የሚሉት እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች “በየትኛውም ውድድር ላይ ያልታዩ፣ ነገር ግን በነበረ ብቻ የተመረጡ ተጫዋቾች ከበረኞች ጀምሮ በብሔራዊ ቡድኑ እንዲካተቱ ተደርጓል:: ዓመቱን ሙሉ ለክለባቸው የተጫወቱ ተጫዋቾች አሉ:: አሰልጣኙ ግን እነዚህ ተጫዋቾች ሊመለከቷቸው አልፈቀዱም” ሲሉ ነው የሚተቿቸው::

የአሰልጣኝ ሰውነትን አስተያየት ለማካተት ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ አድርገንላቸው በስብሰባ ምክንያት ጊዜ እንደሌላቸው ገልፀውልናል:: በተያያዘ ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅሎ የነበረው ሳላዲን ሰይድ በቀጣይ ከክለቡ ጋር ስለሚኖረው ቆይታ ለመነጋገር ተመልሶ ወደ ግብፅ ማምራቱ ታውቋል::

ለለንደን ኦሊምፒክ ቃል ከተገባው 46 ሚሊዮን ብር ገቢ ያልተደረገ እንዳለ ተጠቆመ

ስለ ልዑካን ቡድኑ ማብራርያ የጠየቁ አሉ46 ሚሊዮን ብር ሲሆን፣ ከዚህ ገንዘብ ውስጥ ገቢ እንደተደረገ የሚታመነው 21 ሚሊዮን ብር አካባቢ ነው:: ከቀረው ገንዘብ ውስጥ በዓይነትም ቃል የተገባ መኖሩና በኤስኤምኤስ ደግሞ ወደ 21.1 ሚሊዮን ብር መገኘቱ፣ ከዚህም ውስጥ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለማስታወቂያና ለመሳሰሉት 4.1 ሚሊዮን ብር እንደከፈለ፣ በተመሳሳይም ብሔራዊ ሎተሪ ድርሻውን አስራ አምስት ከመቶ፣ ማለትም ወደ 3.3 ሚሊዮን ብር ገደማ መውሰዱን ያስረዳሉ::

ለብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድኑ በጥሬ ገንዘብም ይሁን በዓይነት ቃል የገቡ ግለሰቦችና ድርጅቶች በቃላቸው መሠረት ክፍያ እንዳልፈፀሙ፤ ምክንያታቸው ደግሞ በለንደን ኦሊምፒክ ላይ ከተወዳዳሪው ይልቅ የልዑካን ቡድኑ ቁጥር ከፍተኛ ሆኖ መገኘቱ፣ ለዚያም የሚመለከተው አካል ተገቢውን ማብራርያ ሊሰጥበት እንደሚገባ ጭምር መጠየቃቸውን ይገልፃሉ::

በዋናነትም ወደ ለንደን የሚያመራውን ብሔራዊ ልዑክ አስመልክቶ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የኢትዮጵያን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ነው ተብሎ ቢታመንም፣ ነገር ግን በወቅቱ ኃላፊነቱን ሙሉ ለሙሉ የወሰደው ፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን መሆኑን የገለፁት ምንጮቹ፣ ከኦሊምፒክ መልስ ከስፖርት ቤተሰቡም ሆነ ከሚመለከተው አካል ለቀረበው ቅሬታ በተገቢው መንገድ ማብራርያ መስጠት የሚገባው ይኼው መንግሥታዊ ተቋም ነበር:: ይሁንና እስከዛሬም በጉዳዩ ዙርያ ምንም ያለው ነገር እንደሌለ ጭምር ያስረዳሉ::

ይህንኑ ተከትሎ ለብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድኑ ቃል የተገባው ገንዘብ እስከአሁን ተጠቃሎ እንዳይገባ ምክንያት ስለመሆኑም ይገልፃሉ:: ስለጉዳዩ የስፖርት ኮሚሽን ኃላፊዎችን ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም::

በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ታምራት በቀለ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጉዳዩን አስመልክቶ እስከሚቀጥለው ሳምንት ባለው ጊዜ ውስጥ መግለጫ ለመስጠት ቅድመ ሁኔታዎችን እያመቻቸ መሆኑን ተናግረው ዝርዝሩን ከመግለፅ ተቆጥበዋል::

የብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ምርጫ በወቅታዊ ብቃት ላይ እንዲያተኩር ተጠየቀ

አዲሱ የብሔራዊ ቡድኑ ዓርማ

ከለንደን ኦሊምፒክ ፍጻሜ በኋላ አዲስ አበባ የተመለሰው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ልዑክ

Page 44: reporter3 ቀን 2005 |ገጽ 1 ነፃ ፕሬስ ነፃ ሐሳብ ነፃ መንፈስ FREE PRESS FREE SPEECH FREE SPIRIT በውስጥ ገጽ 2 ወደ ገጽ 11 ዞሯል ታህሳስ

ገጽ 44|

www.ethiopianreporter.com

| ረቡዕ | ታህሳስ 3 ቀን 2005

የዲዛይንና ዝግጅት በሚዲያ ኮምዩኒኬሽን ሴንተር አሳታሚ የሚዲያና ኮምዩኒኬሽን ሴንተር አታሚ፡ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ክ/ከተማ፡ አራዳ ቀበሌ፡ 17 የቤት ቁጥር፡ 984

ማስታ

ወቂያ

በብርሃኑ ፈቃደ

ኢትዮ ቴሌኮምን በማስተዳደር ላይ ያለው የፈረንሳዩ ኩባንያ የአገሪቱን ቴሌኮም ማኔጅመንት ወስዶ ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር ሲያስተዳደር ቢቆይም፣ የቀጣይነቱ ዕጣ ፈንታ በዚህ ሳምንት ይወሰናል:: ለዚህም የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ሚኒስቴር በይፋ የሚሰጠው መግለጫ እንደሚጠበቅ ታውቋል::

ፍራንስ ቴሌኮም የማኔጅመንቱን ሥራ ይዞ መቀጠል አለመቀጠሉን መንግሥት ይፋ እንደሚያደርግ ቢገለጽም፣ ከወዲሁ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ግን የኩባንያውን መሰናበት የሚያመላክቱ ናቸው:: መንግሥት ከኩባንያው ይጠብቅ የነበረውን የኔትወርክ አገልግሎት አሰጣጥና ጥራት እንደሚፈልገው አለማግኘቱ ከምክንያቶቹ መካከል የሚጠቀሱ ናቸው ተብሏል:: ፍራንስ ቴሌኮም በዚህ ጉዳይ ላይ ዛሬ ማብራርያ እንደሚሰጥ ይጠበቃል::

ፍራንስ ቴሌኮም ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት የቀድሞውን የኢትዮጵያ ቴሌኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬሽን ማኔጅመንት በመረከብ ሥራውን የጀመረው 30 ሚሊዮን ዩሮ ተከፍሎት ነው:: ፍራንስ ቴሌኮም ከኮርፖሬሽኑ ማኔጅመንቱን ከተረከበ በኋላ በተካሄደው የሥራ መደብ ለውጥ ከአምስት ሺሕ በላይ ሠራተኞች መቀነሳቸው ይታወሳል:: በዚህም ምክንያት ሠራተኞች ከፍተኛ ቅሬታ ሲያቀርቡ ነበር::

በሌላ በኩል የኔትወርክ ዘርፉን ከቻይናው ዜድቲኢ ጋር ተቀላቅሏል የተባለለት ሌላው የቻይና ኩባንያ ሁዋዌ ገና በሒደት ላይ ያለ እንጂ፣ ሙሉ ለሙሉ አለመግባቱን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ለሪፖርተር አስታውቀዋል:: ኩባንያው ከዜድቲኢ ጋር የሚጋራውን የኔትወርክ ዝርጋታ ዘርፍ መንግሥት ገና እያየው እንደሆነ ሚኒስትሩ ቢያስታውቁም፣ ኩባንያው 1.5 ቢሊዮን ብር በሚሆን ካፒታል የቴሌኮም ኢንዱስትሪውን ለመቀላቀል ጫፍ እንደደረሰ መረጃዎች ይጠቁማሉ::

በተደጋጋሚ እየተከሰተ ተጠቃሚዎችን የሚያማርረው የሞባይል ስልክ ኔትወርክ መቆራረጥ በተለይ በከፋ ሁኔታ በሚከሰትባቸው አካባቢዎች ላይ ያረጁ የቴሌኮም መስመሮች በአዲስ ካለመተካታቸው ጋር እንደሚያያዝ

የኢትዮ ቴሌኮም አስተዳደር ዕጣ ፈንታ በዚህ ሳምንት ይወሰናል

ሚኒስትሩ መሠረተ ልማቱ በአግባቡ በተዘረጋላቸው አካባቢዎችም ላይ የኔትወርክ ጥራት ችግር እንደሚከሰት አስታውሰው፣ በአገሪቱ ገና በመገንባት ላይ ያለ አገልግሎት በመሆኑ ጥራቱ ጊዜ እንደሚፈጅ አስረድተዋል::

በአንዳንድ አካባቢዎች የሚታየው የከፋ የኔትወርክ ችግር ሙሉ ለሙሉ ተበላሽቷል ወይም አገልግሎት መስጠት አይችልም የሚባልበት ደረጃ ላይ እንዳልሆነም አሳስበዋል:: በየጊዜው እየተሻሻለ መሄድ የሚኖርበት የቴሌኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ እንደመሆኑ፣ ጥራቱም በዚያው መጠን እየተሻሻለ መሄድ እንደሚገባው ዶክተር ደብረጽዮን አስታውቀው፣ ኢትዮ ቴሌኮም ባለው የኔትወርክ መሠረተ ልማት መጠን አገልግሎቱን በጥራት ሊያዳርስ እንደሚገባው አሳስበዋል:: ምንም እንኳ ኢትዮ ቴሌኮም በተዘረጋለት መጠን በአግባቡ አገልግሎት አንዲሰጥ በሚኒስቴሩ እንደሚነገረው ዶክተር ደብረጽዮን ቢናገሩም፣ የተሟላ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ያልተመቻቹ ሥራዎች መኖራቸውን ግን አልሸሸጉም::

በአገሪቱ በአሁኑ ወቅት 20 ሚሊዮን ያህል የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች እንዳሉ ሲገለጽ፣ በ2007 ዓ.ም. 45 ሚሊዮን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል:: ኢንተርኔትን በሞባይልና በኬብል የማዳረሱ ሥራም 3.6 ሚሊዮን ተገልጋዮች እንዳሉት ዶክተር ደብረጽዮን አስታውቀዋል:: ከዚህ ውስጥ በሞባይል ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር 3.4 ሚሊዮን እንደሆነ አስታውሰው፣ በአጠቃላይ የተመዘገቡት 3.6 ሚሊዮን የኢንተርኔት ተጠቃሚዎቹ ቁጥር በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ የተቀመጠው መጠን ላይ እንደደረሰ ገልጸዋል::

የቴሌኮም አገልግሎት ተደራሽነትን በተመለከተ በመላው ኢትዮጵያ 64 በመቶ የሞባይል አገልግሎት እንደተዳረሰ፣ በገጠሩ አካባቢ ገመድ አልባ ስልክ ተጠቃሚዎች ቁጥር 73 በመቶ

መድረሱንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል:: በአገሪቱ ሽፋን ያላገኙ ቦታዎች ከ14 በመቶ እንደማይበልጡ ገልጸው፣ ሽፋኑ የመስፋፋቱን ያህል አገልግሎቱ በጥራት የመዳረሱ ሥራ ግን ሳያቋርጥ መቀጠል እንደሚገባው አስታውቀዋል::

በአገሪቱ የቴሌኮም አግልግሎቱ የማይነካካቸው ዘርፎች ባይኖሩም ባንኮች፣ ምርት ገበያ፣ ሆቴሎችና ሌሎችም በአገልግሎቱ መቆራረጥ ሳቢያ ክፉኛ የሚቸገሩ ናቸው:: መንግሥት በሰከንድ 622 ሜጋ ባይት ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ቴክኖሎጂን እየተጠቀመ እንደሚገኝ አስታውቋል:: ሆኖም በኢንተርኔት አማካይነት የሚተላለፍ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ለመከታተል፣ አሊያም በዩቲዩብ አማካይነት ቪዲዮ ለመመልከት (ያውም በብሮድባንድ ኢንተርኔት) የወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታ ለዚህ አገልግሎት እንደማይመች አመላካች ከሆኑ መረጃዎች አንዱ፣ ይኼው በኢንተርኔት አማካይነት የቪዲዮ መረጃዎችን በፍጥነት ማግኘትን የተመለከተው ሲሆን፣ በመላው ዓለም በሰኮንድ ከሰባት ሜጋ ባይት በላይ ፍጥነት ያለው ይህ አገልግሎት በኢትዮጵያ ከሁለት ሜጋ ባይት በታች ሆኖ ይገኛል::

ዶክተር ደብረጽዮን ገልጸዋል:: ዶክተር ደብረጽዮን እንዳስታወቁት፣ በከፍተኛ ደረጃ

የቴትወርክ ችግር የሚያጋጥማቸው አካባቢዎች ላይ መቀየር ያለባቸው መሠረተ ልማቶች ባለመቀየራቸው ሳቢያ የሞባይል ስልክም ሆነ የኢንቴርኔት አገልግሎት ችግር እያጋጠመ ይገኛል:: ሆኖም በቅርቡ የተከሰተው ከፍተኛ ችግር ከኅዳር 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ በኬንያ በኩል የሚገባው ኦፕቲካል ፋይበር ዓለም አቀፍ መስመሩ ጉዳት ስለደረሰበት እንደሆነ ኢትዮ ቴሌኮም ማስታወቁ ይታወሳል::

የኔትወርክ መቆራረጥ የሚከሰተው ያረጁ የቴሌ መስመሮች ባለመቀየራቸው ነው ተባለ

ዶክተር ደብረጽዮን